ሩሲያ እና ናሚቢያ በዩራኒየም ክምችት ላይ በጋራ ለመሥራት ተወያይተዋል - ሮሳቶም
17:16 14.01.2026 (የተሻሻለ: 17:24 14.01.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ሩሲያ እና ናሚቢያ በዩራኒየም ክምችት ላይ በጋራ ለመሥራት ተወያይተዋል - ሮሳቶም
ሩሲያ እና ናሚቢያ የኒውክሌር ኃይልን ለሰላማዊ ዓላማ ለመጠቀም በሚያስችል የትብብር ስምምነት ዝግጅት ላይ መወያየታቸውን የሩሲያ መንግሥታዊ የኒውክሌር ኤጀንሲ (ሮሳቶም) በዛሬው ዕለት አስታውቋል።
የኤጀንሲው መግለጫ እንደሚያሳየው፣ የሮሳቶም ባለሥልጣናት እና በውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሴልማ አሺፓላ-ሙሳቪ የተመራው የናሚቢያ ልዑክ በትናንትናው ዕለት በሞስኮ ውይይት አድርገዋል።
ሮሳቶም በናሚቢያ የሚያደርገውን የዩራኒየም ፍለጋ ሥራ በጎርጎሮሳዊያኑ 2026 ለማጠናቀቅ እና በ2029 ደግሞ ማዕድኑን ማውጣት ለመጀመር ማቀዱን ቀደም ብሎ ለስፑትኒክ አስታውቆ ነበር።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X