አሜሪካ በቬንዙዌላ ላይ የምትወስዳቸው እርምጃዎች ‘ተቀባይነት የሌለው የዓለም አቀፍ ሕግ ግልጽ ጥሰት ነው’ ሲሉ ሰርጌ ላቭሮቭ ገለጹ

ሰብስክራይብ

አሜሪካ በቬንዙዌላ ላይ የምትወስዳቸው እርምጃዎች ‘ተቀባይነት የሌለው የዓለም አቀፍ ሕግ ግልጽ ጥሰት ነው’ ሲሉ ሰርጌ ላቭሮቭ ገለጹ

​የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ለጋዜጠኞች እንደተናገሩት፣ ሞስኮ በቬንዙዌላ ወቅታዊ ሁኔታ ላይ ያላት አቋም ጽኑ መሆኑን ገልጸው፣ በሩሲያ እና በቬንዙዌላ መካከል ያለውን ረጅም ታሪክ ያለው ጠንካራ ስትራቴጂያዊ ግንኙነት አጉልተዋል።

ላቭሮቭ በመግለጫቸው ያነሷቸው ሌሎች ሃሳቦች፦

🟠 አሜሪካ ከኢራን ጋር በሚደረግ ማንኛውም የንግድ ልውውጥ ላይ የ25 በመቶ ቀረጥ መጣሏ ተዓማኒነት እንደሌላት ያሳያል፡፡

🟠 የትኛውም ውጫዊ አካል የሩሲያ እና የኢራንን ግንኙነት ተፈጥሮን (መሠረት) ሊለውጥ አይችልም፡፡

​🟠 የአሜሪካ የማዕቀብ ፖሊሲ ቀጣይነት የሌለው ከመሆኑም በላይ በዓለም አቀፍ ግንኙነቶች ላይ ጥልቅ ቀውስ ያስከትላል፡፡

​🟠 ምዕራባውያን ስለ ተኩስ አቁም ሃሳብ ማውራታቸው ለዩክሬን ተጨማሪ ጊዜ የመግዛት ሙከራ ነው፡፡

🟠 በፑቲን፣ በዊትኮፍ እና በኩሽነር መካከል የተደረጉት ስብሰባዎች ፍሬያማ እና የዩክሬንን ቀውስ ዋና መንስኤዎች ለመፍታት የታለሙ ነበሩ፡፡

🟠 አሜሪካ ዩክሬንን ወደ ኔቶ ለማስገባት የሚደረጉ ማናቸውንም ጥረቶች የማስቆም ዕቅድ አላት፤ ሩሲያም ይህንን ታውቃለች፡፡

🟠 ፑቲንበዩክሬን ጉዳይ ላይ ለሚደረጉ ቁምነገር ያላቸው ድርድሮች ሩሲያ ዝግጁ መሆኗን በተደጋጋሚ አረጋግጠዋል፡፡

​🟠 በዩክሬን ጉዳይ ላይ የሩሲያ እና የአሜሪካ ግንኙነት በአላስካ ንግግሮች ወቅት በተጣለው ጠንካራ መሠረት ላይ የተገነባ ነው፡፡

🟠 ሩሲያ የአሜሪካ ተወካዮች ከአውሮፓውያኑ "የፈቃደኞች ጥምረት" ጋር ካደረጉት ስብሰባ ያገኙትን ግንዛቤ የማወቅ ፍላጎት አላት።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0