ሱዳን እየተካሄደ በሚገኘው ግጭት ወቅት የተዘረፉ 570 ታሪካዊ ቅርሶች ማስመለሷን መንግሥት አስታወቀ
13:25 14.01.2026 (የተሻሻለ: 13:34 14.01.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ሱዳን እየተካሄደ በሚገኘው ግጭት ወቅት የተዘረፉ 570 ታሪካዊ ቅርሶች ማስመለሷን መንግሥት አስታወቀ
ቅርሶቹ፣ የመካነ-መቃብር ሐውልቶች፣ በስነ-ጥበብ ያጌጡ የአበባ ማስቀመጫዎች፣ የነሐስ የቤት ዕቃዎች፣ የተቀረጹ ድንጋዮች እና ትናንሽ ጥንዚዛ-መሳይ ክታቦች ይገኙበታል። ከቅድመ-ታሪክ እስከ እስልምና ዘመን የሚዘልቁ እነዚህ ጥንታዊ ቅርሶች በባህል ሚኒስትሩ ካሊድ አል-አይሲር አማካኝነት በፖርት ሱዳን በይፋ ለዕይታ ቀርበዋል።
ባለስልጣናት እንዳስታወቁት፣ ሀገሪቱ ካለፈው ሚያዝያ ጀምሮ በጎረቤት አገራት በኩል በኮንትሮባንድ የወጡ ቅርሶችን ለማስመለስ ከኢንተርፖል እና ከዩኔስኮ ጋር በትብብር እየሠራች ትገኛለች።
በሱዳን መደበኛው ጦር እና በአማፂው የፈጥኖ ደራሽ ሚሊሻ መካከል በተቀሰቀሰው የትጥቅ ግጭት፣ በጎርጎሮሳዊያኑ 2023 ብሉ ናይል የሚገኘው የካርቱም ብሔራዊ ሙዚየም ሙሉ በሙሉ ተዘርፎ ነበር፡፡ ከስርቆት የተረፈው አንድ ክፍል ብቻ ነው። በተጨማሪም በሀገሪቱ የሚገኙ በርካታ ሌሎች ሙዚየሞችም ከፍተኛ ጉዳት ደርሶባቸዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X



