ሩሲያ እና ናሚቢያ በዊንድሆክ ለሚካሄዱ የከፍተኛ ደረጃ ውይይቶች እየተዘጋጁ ነው

ሰብስክራይብ

ሩሲያ እና ናሚቢያ በዊንድሆክ ለሚካሄዱ የከፍተኛ ደረጃ ውይይቶች እየተዘጋጁ ነው

​ሞስኮ እና ዊንድሆክ በጎርጎሮሳዊያኑ 2026 በናሚቢያ ለሚካሄደው 11ኛው የሩሲያ-ናሚቢያ በይነ-መንግሥታት የንግድ እና ኢኮኖሚ ትብብር ኮሚሽን ስብሰባ የመጨረሻ ዝግጅቶችን እያጠናቀቁ ነው።

ውሳኔው የተረጋገጠው የኮሚሽኑ ሊቀ-መናብርት በሆኑት የሩሲያ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ዩሪ ትሩትኔቭ እና የናሚቢያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሴልማ አሺፓላ-ሙሳቪ መካከል በሞስኮ ባደረጉት ስብሰባ ላይ መሆኑን ትሩትኔቭ የፕሬስ አገልግሎት አስታውቋል፡፡

​ትሩትኔቭ በሁለቱ አገራት መካከል ያለውን “ዘላቂ ወዳጅነት” አበክረው የገለጹ ሲሆን፣ የናሚቢያ ፕሬዝዳንት ናንዲ-ንዳይትዋ ወደ ሩሲያ በተደጋጋሚ ያደረጉትን ጉብኝት እና ለሞስኮ ያላቸውን ቀጣይነት ያለው በጎ አመለካከት አስታውሰዋል። አክለውም፣ አሺፓላ-ሙሳቪ ለፕሬዝዳንቷ የግል ምስጋናቸውን እና መልካም ምኞታቸውን እንዲያደርሱላቸው ጠይቀዋል።

​ሁለቱ ወገኖች የንግድ ልውውጥን ማሳደግ፣ በጂኦሎጂ እና በማዕድን ቁፋሮ፣ በትምህርት ዘርፍ ስላለው ትብብር የተወያዩ ሲሆን፤ በ2026 ከሚካሄደው የኮሚሽኑ ስብሰባ ጎን ለጎን በሩሲያ ድጋፍ የሚደረግ የንግድ ፎረም ለማካሄድ ተስማምተዋል።

​አሺፓላ-ሙሳቪ በዛሬው ዕለት ረፈድ ብሎ ከሰርጌ ላቭሮቭ ጋር ውይይት የሚያደርጉ ሲሆን፣ በጋራ ጋዜጣዊ መግለጫም እንደሚሰጡ ይጠበቃል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0