በሰሜን ምዕራብ ሩሲያ ከሚገኘው የቪሶትስክ ወደብ 44 ሺህ ቶን ስንዴ ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ኬንያ ተላከ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱበሰሜን ምዕራብ ሩሲያ ከሚገኘው የቪሶትስክ ወደብ 44 ሺህ ቶን ስንዴ ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ኬንያ ተላከ
በሰሜን ምዕራብ ሩሲያ ከሚገኘው የቪሶትስክ ወደብ 44 ሺህ ቶን ስንዴ ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ኬንያ ተላከ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 13.01.2026
ሰብስክራይብ

በሰሜን ምዕራብ ሩሲያ ከሚገኘው የቪሶትስክ ወደብ 44 ሺህ ቶን ስንዴ ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ኬንያ ተላከ

በሩሲያ የፌደራል የግብርና ምርቶች ደህንነት እና ጥራት ግምገማ ማዕከል የሴንት ፒተርስበርግ ቅርንጫፍ ዳይሬክተር አኒታ ሚሌኪና እንደገለጹት፣ "እ.ኤ.አ. በ2025 በቅርንጫፋችን በኩል  የእህል ምርቶችን በማስገባት ኬንያ 18ኛዋ ሀገር ሆናለች፤ ከሀገራቱ መሃከል 9ኙ የአፍሪካ ሀገራት ናቸው። ይህም የአፍሪካ ሀገራት ለሩሲያ እህል ያላቸውን ፍላጎት እና በባልቲክ ባህር ወደቦች በኩል የሚደረገውን የወጪ ንግድ መስመር እድገት ያሳያል" ብለዋል።

የተላከው ስንዴ የኬንያን መስፈርቶች ሙሉ በሙሉ እንደሚያሟላ የላቦራቶሪ ምርመራዎች ማረጋገጣቸውን ማዕከሉ አስታውቋል።

​ከምርመራው በኋላ ለጭነቱ የሙከራ ፕሮቶኮሎች፣ የዕፅዋት ጤና የምስክር ወረቀት እና የኳራንቲን የፀረ-ተባይ ማጥፊያ ሪፖርት ተሰጥቷል።

በጎርጎሮሳዊያኑ 2025 ሩሲያ ከ1.8 ሚሊዮን ቶን በላይ የእህል ምርቶችን ወደ ውጭ የላከች ሲሆን፣ የስንዴ ምርቷ 78 በመቶውን (ከ1.3 ሚሊዮን ቶን በላይ) ይሸፍናል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0