ቻይና እና የአፍሪካ ሕብረት ስትራቴጂያዊ መተማመንን የሚያጠናክሩበትና ትብብርን የሚያሳድጉበት ጊዜ አሁን ነው - የቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር
19:02 13.01.2026 (የተሻሻለ: 19:04 13.01.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ቻይና እና የአፍሪካ ሕብረት ስትራቴጂያዊ መተማመንን የሚያጠናክሩበትና ትብብርን የሚያሳድጉበት ጊዜ አሁን ነው - የቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር
ቻይና ከአፍሪካ ሀገራት ጋር በመሆን ተቋማዊ የሆኑ የትብብር መድረኮችን ለመገንባት ዝግጁ መሆኗን ዋንግ ዪ ለቻይና መገናኛ ብዙኃን ገልጸዋል።
ቤጂንግ አፍሪካውያን እንደየፍላጎታቸው የራሳቸውን የልማት ጎዳና እንዲከተሉ፣ ህዝቦቻቸውን ተጠቃሚ እንዲያደርጉ እና ሀብቶቻቸውን ሙሉ በሙሉ እንዲጠቀሙ ለመርዳት ፈቃደኛ መሆኗንም አክለዋል።
ዋንግ ዪ ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ለአፍሪካ ከፍተኛ ትኩረት እንዲሰጥ እና በአኅጉሪቱ ላይ ያለውን ኢንቨስትመንት እንዲያሳድግ አሳስበዋል።
ሚኒስትሩ አክለውም፣ የዓለም ዘመናዊነት ሊረጋገጥ የሚችለው ቻይና እና አፍሪካ በጋራ ወደ ዘመናዊነት ሲጓዙ ብቻ ነው፤ ያለ አፍሪካ ዘመናዊነት፣ የዓለም ዘመናዊነት ሊታሰብ አይችልም ብለዋል።
በሰው ሠራሽ አስተውሎት የበለፀገ ምስል
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X