ኢትዮጵያ ካዛኪስታንና ኖርዌይን በመቅደም ከዓለም 10 ቀዳሚ የቢትኮይን አልሚዎችን ተርታ ተቀላቀለች
18:39 13.01.2026 (የተሻሻለ: 18:44 13.01.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ኢትዮጵያ ካዛኪስታንና ኖርዌይን በመቅደም ከዓለም 10 ቀዳሚ የቢትኮይን አልሚዎችን ተርታ ተቀላቀለች
እንደ "ሃሽራቴ ኢንዴክስ" የ2026 የመጀመሪያ ሩብ ዓመት ዓለም አቀፍ ሪፖርት፣ ኢትዮጵያ የቢትኮይን ልማት ዓለም አቀፍ ገበያ 2.6 በመቶ ድርሻ ይዛለች።
የሀገሪቱ የማልማት አቅም ባለፈው ሩብ ዓመት ከነበረው በ38 በመቶ በማደግ ከ20 ኤክሃሽስ በሰከንድ ወደ 27.5 ኤክሃሽስ ከፍ ብሏል። ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር ደግሞ የ129 በመቶ እድገት አሳይታለች።
መንግሥት የኤሌክትሪክ አቅርቦትን ለመጠበቅ እና ለቤት ውስጥ ፍጆታ ቅድሚያ ለመስጠት ሲል በሰኔ 2017 ዓ.ም አካባቢ ለአዲስ የቢትኮይን ልማት ፈቃድ መስጠትን ማቆሙ ይታወሳል ሲል የአገር ውስጥ የግል ሚዲያ ዘግቧል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X