በቡርኪና ፋሶ የካቢኔ ሽግሽግ ተደረገ፤ በርካታ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች የስም ለውጥ አድርገዋል

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱበቡርኪና ፋሶ የካቢኔ ሽግሽግ ተደረገ፤ በርካታ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች የስም ለውጥ አድርገዋል
በቡርኪና ፋሶ የካቢኔ ሽግሽግ ተደረገ፤ በርካታ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች የስም ለውጥ አድርገዋል - Sputnik አፍሪካ, 1920, 13.01.2026
ሰብስክራይብ

በቡርኪና ፋሶ የካቢኔ ሽግሽግ ተደረገ፤ በርካታ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች የስም ለውጥ አድርገዋል

​ በትናንትናው ዕለት በታወጀው አዋጅ የቡርኪና ፋሶ አዲስ ካቢኔ 22 አባላትን ይዟል።

​ዋና ዋና ለውጦች የሚከተሉትን ያካትታሉ፦

🟠 የመከላከያ ሚኒስቴር ወደ የጦርነት እና የሀገር ፍቅር መከላከያ ሚኒስቴር የተቀየረ ሲሆን፤ በሜጀር ጄኔራል ሴሌስቲን ሲምፖሬ መመራቱን ይቀጥላል።

🟠 የመንግስት አገልግሎት እና ሰራተኛ ሚኒስቴር ስሙ ወደ የሕዝብ አገልጋዮች ሚኒስቴር የተቀየረ ሲሆን፤ በማቲያስ ትራኦሬ ይመራል።

​🟠 የቤት እና የከተማ ፕላን ሚኒስቴሮች ተቀናጅተው የሀገር ግንባታ ሚኒስቴር የተባሉ ሲሆን፤ በሚካኢሉ ሲዲቤ ይመራሉ።

​▪ ጠቅላይ ሚኒስትር ሪምታልባ ዣን ኢማኑኤል ኦውድራጎ በመንግስት መሪነት ቦታቸው ላይ ይቆያሉ።

​▪ ካራሞኮ ዣን ማሪ ትራኦሬ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሆነው በድጋሚ ተሹመዋል።

​▪ ኤዳሶ ሮድሪግ ባያላ የፍትህ ሚኒስትር ሆነው ቀጥለዋል።

​የስፖርት ሚኒስትሩ ሮላንድ ሶምዳ ከኃላፊነታቸው የለቀቁ ሲሆን፣ አሁን ላይ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ በአኒክ ሊዲ ጁማ ፒክቡጉም ዚንጌ ዋታራ ይመራል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0