የአውሮፓውያን በግሪንላንድ ወታደር የማሰማራት ዕቅድ "ፖለቲካዊ ትያትር" ቢሆንም ሊሳካ ይችላል - ተንታኝ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱየአውሮፓውያን በግሪንላንድ ወታደር የማሰማራት ዕቅድ "ፖለቲካዊ ትያትር" ቢሆንም ሊሳካ ይችላል - ተንታኝ
የአውሮፓውያን በግሪንላንድ ወታደር የማሰማራት ዕቅድ ፖለቲካዊ ትያትር ቢሆንም ሊሳካ ይችላል - ተንታኝ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 13.01.2026
ሰብስክራይብ

የአውሮፓውያን በግሪንላንድ ወታደር የማሰማራት ዕቅድ "ፖለቲካዊ ትያትር" ቢሆንም ሊሳካ ይችላል - ተንታኝ

"ዋናው ዓላማ አሜሪካ ግሪንላንድን ወደ ራሷ ግዛት ለማጠቃለል ለምታደርገው ማንኛውም ዕቅድ መከላከያ መፍጠር መሆኑ ግልጽ ነው" ሲሉ ስዊድናዊው የመከላከያ ተንታኝ ሚካኤል ቫልተርሰን ለስፑትኒክ ተናግረዋል። ተንታኙ፣ ይህንን የተናገሩት እንግሊዝ እና ጀርመን የሚመሩት የኔቶ ኃይሎች በግሪንላንድ ስለማስፈር የሚደረገውን ንግግር አስመልክቶ ነው።

"ይህ እርምጃ ወታደራዊ ሳይሆን በዋናነት ፖለቲካዊ ፋይዳ ያለው ነው፤ ምክንያቱም ጥቂት የአውሮፓ የምድር ጦር ኃይሎችን ማሸነፍ ለአሜሪካ ጦር ምንም ችግር ስለማይሆን ነው። ነገር ግን በአውሮፓ አጋሮች ላይ የሚወሰድ ማንኛውም ወታደራዊ እርምጃ በአውሮፓ ላይ የሞት ፍርድ እንደመፍረድ ይቆጠራል፤ እንዲሁም የቆየውን የአትላንቲክ ማዶ ግንኙነት ይበጥሳል" ሲሉ ቫልተርሰን አጽንኦት ሰጥተዋል።

🟠 የኃይሉ መሰማራት እውን ቢሆን ራሱ "ጨዋታ ቀያሪ" ባይሆንም፣ በፔንታገን ውስጥ "ወታደራዊ እርምጃን የሚቃወሙ ወገኖችን ሊያጠናክር ይችላል፡፡"

🟠 በሌላ በኩል፣ ይህ እርምጃ በፕሬዝዳንት ትራምፕ የቅርብ አማካሪዎች ዘንድ "አውሮፓውያን ለአሜሪካ ያቀረቡት ተግዳሮት" ተደርጎ ሊወሰድና የተገላቢጦሽ ውጤት ሊያስከትል እንደሚችል ቫልተርሰን አስጠንቅቀዋል።

  "ይህ የሚሆን ከሆነ ደግሞ በአሜሪካ እና በአውሮፓ ግንኙነት ላይ የሚያስከትለው መዘዝ የከፋ ይሆናል" ብለዋል ተንታኙ።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0