የኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለሥልጣን ለሁለት የአቪዬሽን ተቋማት የሥራ ፈቃድ ሰጠ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱየኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለሥልጣን ለሁለት የአቪዬሽን ተቋማት የሥራ ፈቃድ ሰጠ
የኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለሥልጣን ለሁለት የአቪዬሽን ተቋማት የሥራ ፈቃድ ሰጠ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 13.01.2026
ሰብስክራይብ

የኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለሥልጣን ለሁለት የአቪዬሽን ተቋማት የሥራ ፈቃድ ሰጠ

ባለስልጣኑ በኢትዮጵያ አየር ኃይል ስር ለሚገኘው ለከባድ ጥገና ማዕከል እና ለዓለም አቀፍ ካርጎ አቪዬሽን ሰርቪስ (አይፓስ) የአቪዬሽን ጥገና እና የአቪዬሽን ትምህርት የሥራ ፈቃዶችን ሰጥቷል፡፡

ለዓለም አቀፍ ካርጎ አቪዬሽን ሰርቪስ የተሰጠው የሥራ ፈቃድ በአቪዬሽን ማሰልጠኛ አካዳሚ ዘርፍ የተሰማሩ ተቋማትን ቁጥር ወደ አምስት የሚያሳድግ ሲሆን በኢትዮጵያ አየር መንገድ ብቻ ተይዞ የነበረውን የጥገና አገልግልት ለተጨማሪ አንድ ተቋም ክፍት የሚያደርግ ነው።

በሥነ ስርዓቱ ላይ ንግግር ያደረጉት የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚንስትር ዓለሙ ስሜ እንዳሉት፣ በኢትዮጵያ በበረራ አገልግሎት ላይ የተሰማሩ የግል አቪዬሽን ተቋማት ለአውሮፕላኖች ጥገና አገልግሎት ለማግኘት ወደ ውጭ ሃገራት ሄደው ከፍተኛ ወጪ ያወጡ እንደነበር ጠቁመው ለአየር ኃይል ከባድ ጥገና ማዕከል የተሰጠው የሥራ ፈቃድ ይህን ችግር እንሚቀርፍ ገልጸዋል።

ፈቃድ አሰጣጡ ለጥገና አገልግሎት ይወጣ የነበረውን ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ ከማስቀረት ባሻገር የአየር ትራንስፖርት ዘርፍን ለማስፋፋት እና ለማዘመን ያስቀመጠችውን ዕቅድ እውን ለማድረግ የጎላ አስተዋጽኦ እንደሚኖረውም ሚኒስትሩ ተናግረዋል።

በኢትዮጵያ 12 የግል የአየር በረራ አገልግልት የሚሰጡ ተቋማት በሥራ ላይ እንደሚገኙ በዝግጅቱ ላይ መገለፁን የስፑትኒክ አፍሪካ ጋዜጠና ዘግቧል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱ
የኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለሥልጣን ለሁለት የአቪዬሽን ተቋማት የሥራ ፈቃድ ሰጠ - Sputnik አፍሪካ
1/2
© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱ
የኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለሥልጣን ለሁለት የአቪዬሽን ተቋማት የሥራ ፈቃድ ሰጠ - Sputnik አፍሪካ
2/2
1/2
2/2
አዳዲስ ዜናዎች
0