የኦሬሽኒክ ጥቃት የልቮቭ ግዛት አውሮፕላን መጠገኛ ጣቢያን ከጥቅም ውጭ አድርጓል ሲል የሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴር አስታወቀ
19:05 12.01.2026 (የተሻሻለ: 19:14 12.01.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የኦሬሽኒክ ጥቃት የልቮቭ ግዛት አውሮፕላን መጠገኛ ጣቢያን ከጥቅም ውጭ አድርጓል ሲል የሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴር አስታወቀ
ሚኒስቴሩ በመግለጫው ያነሳቸው ዋና ዋና ነጥቦች፦
ጣቢያው የዩክሬን ጦር ኃይሎች አውሮፕላኖችን ለመጠገንና ለማቆየት እንዲሁም ሩሲያ ላይ ለሚሰነዘሩ ጥቃቶች የሚያገለግሉ ድሮኖችን ለማምረት ይውል ነበር።
በጥር 1 ምሽት የተፈጸመው ይህ ጥቃት ማምረቻ ስፍራዎችን፣ የድሮን መጋዘኖችን እና የፋብሪካውን የአየር ማረፊያ መሠረተ ልማት ላይ ጉዳት አድርሷል።
በአጠቃላይ፣ ኢስካንደር እና ካሊብር ሚሳኤሎችን በመጠቀም በተፈጸመው መጠነ-ሰፊ ጥቃት፣ በኪዬቭ የሚገኙ የሁለት ድርጅቶች ማምረቻ ስፍራዎች እና የዩክሬንን ወታደራዊ-ኢንዱስትሪ ማዕከልን የሚደግፉ የኢነርጂ መሠረተ ልማቶች ወድመዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X