የብሪክስ የባሕር ኃይል ልምምዶች ለማንም ስጋት አይፈጥሩም - የደቡብ አፍሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱየብሪክስ የባሕር ኃይል ልምምዶች ለማንም ስጋት አይፈጥሩም - የደቡብ አፍሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር
የብሪክስ የባሕር ኃይል ልምምዶች ለማንም ስጋት አይፈጥሩም - የደቡብ አፍሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር - Sputnik አፍሪካ, 1920, 12.01.2026
ሰብስክራይብ

የብሪክስ የባሕር ኃይል ልምምዶች ለማንም ስጋት አይፈጥሩም  - የደቡብ አፍሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር

​ደቡብ አፍሪካ ከብዙ ሀገራት ጋር ልምምዶችን እንደምታደርግ እና እነዚህ ልምምዶች በማንም ላይ የጦርነት አዋጅ አለመሆናቸውን ሮናልድ ላሞላ ለደቡብ አፍሪካ ሚዲያ ተናግረዋል።

​እነዚህ ልምምዶች ምዕራባውያን ሀገራትን እና አሜሪካን ጨምሮ በዓለም ላይ ላለ ለማንም ሀገር ስጋት አይፈጥሩም ሲሉም ላሞላ አጽንኦት ሰጥተዋል።

​እነዚህ ልምምዶች ሌሎች ሀገራት ከሚያደርጉት ጋር ተመሳሳይነት ያላቸው መደበኛ የባህር ኃይል ልምምዶች ናቸው ብለዋል።

"ለሰላም ፍላጎት 2026" የተሰኘው ዓለም አቀፍ የባህር ኃይል ልምምድ በደቡብ አትላንቲክ የባሕር ወሽመጥ፣ ከ"ኬፕ ኦፍ ጉድ ሆፕ" አቅራቢያ ጥር 1 ተጀምሯል። ልምምዱ ከኢራን፣ ከቻይና፣ ከተባበሩት አረብ ኤምሬትስ፣ ከሩሲያ እና ከደቡብ አፍሪካ የተውጣጡ መርከቦችን ያካተተ ሲሆን ብራዚል፣ ኢንዶኔዢያ እና ኢትዮጵያ ደግሞ በታዛቢነት እየተሳተፉ ነው።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0