ኢትዮጵያ ከ10 ዓመት ባነሰ ጊዜ ውስጥ ከኒውክሌር ቴክኖሎጂ ኃይል ማመንጨት እንደምትጀምር ተዘገበ
12:04 12.01.2026 (የተሻሻለ: 12:14 12.01.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ኢትዮጵያ ከ10 ዓመት ባነሰ ጊዜ ውስጥ ከኒውክሌር ቴክኖሎጂ ኃይል ማመንጨት እንደምትጀምር ተዘገበ
የኒውክሌር ቴክኖሎጂን ለመገንባት ከ10 እስከ 15 ዓመታት የሚፈጅ ቢሆንም፣ ኢትዮጵያ እያደረገች ባለው የቅድመ ዝግጅት ፍጥነት ከተጠቀሰው ባነሰ ጊዜ ውስጥ ወደ ሥራ ለመግባት አቅዳ እየሠራች መሆኑን የኢትዮጵያ የኒውክሌር ኢነርጂ ኮሚሽን አስታውቋል።
ኮሚሽኑ ከተቋቋመ በኋላ አስፈላጊ መሠረተ ልማቶችን የመገንባትና ከጥንቃቄና ደኅንነት አኳያ የሚከናወኑ ተግባራትን እየሠራ መሆኑም ተገልጿል።
የኒውክሌር ልማት ፕሮግራሙ የኃይል አቅርቦትን ከአየር ንብረት ጋር በተጣጣመ መልኩ አስተማማኝ ለማድረግ ያለመ መሆኑን የኮሚሽኑን ባለሥልጣን ጠቅሶ የአገር ውስጥ ሚዲያ ዘግቧል፡፡
ባለፈው መስከረም የኢትዮጵያ መንግሥት ከሩሲያው መንግሥታዊ የኒውክሌር ኃይል ኩባንያ ሮሳቶም ጋር የኒውክሌር ልማት ፕሮጀክት ስምምነት መፈራረሙ ይታወሳል።
በሰው ሠራሽ አስተውሎት የበለፀገ ምስል
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X