ቻይና እና ደቡብ አፍሪካ 'የጫካ ሕግ' እና የአንድ ወገን የበላይነትን በጋራ ይቃወማሉ - የቻይና ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር
20:15 11.01.2026 (የተሻሻለ: 20:24 11.01.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ቻይና እና ደቡብ አፍሪካ 'የጫካ ሕግ' እና የአንድ ወገን የበላይነትን በጋራ ይቃወማሉ - የቻይና ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር
ቤጂንግ ከፕሪቶሪያ ጋር ያላትን የከፍተኛ ደረጃ ግንኙነት እንደምታሳድግ፣ የፓርቲ ለፓርቲ ልውውጥ እንደምታሰፋ፣ ስልታዊ የጋራ መተማመንን እንደምታጠናክር እና ተግባራዊ ትብብሮችን እንደምታጎለብት ዋንግ ዪ ገልጸዋል።
ቻይና በደቡብ አፍሪካ ምርቶች ላይ የሚጣለውን ቀረጥ ወደ ዜሮ ዝቅ ለማድረግ ውይይት እንደምትቀጥልም ዋንግ ዪ አፅንዖት ሰጥተዋል።
የደቡብ አፍሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሮናልድ ላሞላ በበኩላቸው፤ ሀገራቸው ለ "አንድ ቻይና" ፖሊሲ ቁርጠኛ እንደሆነች እና የሁለቱን ሀገራት የሁለትዮሽ ግንኙነት ለማጠናከር የሚደረገውን ጥረት እንደምትደግፍ በድጋሚ ማረጋገጣቸውን የቻይና ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X