አፍሪካ በማዱሮ እስራት ዙሪያ ትራምፕን በኅብረት ተቃውመዋል - ሚዲያ
19:50 11.01.2026 (የተሻሻለ: 20:04 11.01.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
አፍሪካ በማዱሮ እስራት ዙሪያ ትራምፕን በኅብረት ተቃውመዋል - ሚዲያ
የአፍሪካ ሀገራት በተናጠል እንዲሁም ዋና ዋና ክልላዊ ድርጅቶች፤ ኢኮዋስ እና የአፍሪካ ኅብረትን ጨምሮ፤ የማዱሮን እስራት “በሰፊው አውግዘዋል” ሲል የምዕራባውያን የዜና አውታር ዘግቧል።
አሜሪካ ታህሳስ 25 ቀን ቬንዙዌላ ላይ በሰነዘረችው ከፍተኛ ጥቃት ማዱሮ እና ባለቤታቸውን በማፈን ወደ ኒውዮርክ ወስዳለች። ትራምፕ “በዕፅ ሽብርተኝነት” ክስ በአሜሪካ ለፍርድ እንደሚቀርቡ ተናግረዋል።
የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ከቬንዙዌላ ሕዝብ ጋር አብሮነቱን በመግለፅ፤ ማዱሮ እና ባለቤታቸው እንዲፈቱ እንዲሁም ተጨማሪ መካረሮችን ማስቀረት እንደሚገባ ጥሪ አቅርቧል።
በሰው ሠራሽ አስተውህሎት የበለፀገ ምሥል
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X