የቤት ግንባታ ችግርን የሚቀርፍ አፈርን ከሲሚንቶ ጋር በመቀላቀል ደረጃውን የጠበቀ ቤት ለመገንባት የሚያስችል ጥናት መጠናቀቁ ተገለፀ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱየቤት ግንባታ ችግርን የሚቀርፍ አፈርን ከሲሚንቶ ጋር በመቀላቀል ደረጃውን የጠበቀ ቤት ለመገንባት የሚያስችል ጥናት መጠናቀቁ ተገለፀ
የቤት ግንባታ ችግርን የሚቀርፍ አፈርን ከሲሚንቶ ጋር በመቀላቀል ደረጃውን የጠበቀ ቤት ለመገንባት የሚያስችል ጥናት መጠናቀቁ ተገለፀ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 11.01.2026
ሰብስክራይብ

የቤት ግንባታ ችግርን የሚቀርፍ አፈርን ከሲሚንቶ ጋር በመቀላቀል ደረጃውን የጠበቀ ቤት ለመገንባት የሚያስችል ጥናት መጠናቀቁ ተገለፀ

በሐረሪ፣ በድሬዳዋ እና በጅግጅጋ አካባቢዎች የሚገኘውን አፈር ለቤት ግንባታ በሚውል መልኩ በማዘጋጀት ዙሪያ ከሐሮማያ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር የተደረገው ጥናት መጠናቀቁን የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ማኔጅመንት ኢንስቲትዩት አስታውቋል።

የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ታምራት ሙሉ፤ "ቴክኖሎጂው አፈርን ከትንሽ ሲሚንቶ ጋር በመቀላቀል ደረጃውን የጠበቀ ቤት ለመገንባት የሚያስችል ነው" ሲሉ ለሀገር ውስጥ ሚዲያ ተናግረዋል።

ጥናቱ ሁሉንም የኢንጂነሪንግ መስፈርቶች አሟልቶ በቤተ-ሙከራ ተረጋግጧል የተባለ ሲሆን በአሁኑ ወቅት "ለአካባቢያዊ ችግር አካባቢያዊ መፍትሔ" በሚል ስትራቴጂ ለመጨረሻ ማረጋገጫ ለውይይት መቅረቡ ተመላክቷል።

ግንባታዎች ሙሉ በሙሉ በሲሚንቶ ላይ ብቻ የተንጠለጠሉ እንዳይሆኑ በማድረግ እና የግንባታ ወጪን በመቀነስ ከ6 ሚሊዮን በላይ ለሚሆኑ የሐረሪ፣ ድሬዳዋ እና ጅግጅጋ ነዋሪዎች የቤት ግንባታ ችግርን የሚቀርፍ መፍትሔ ይዞ መቅረቡን ዋና ዳይሬክተሩ ተናግረዋል።

በሰው ሠራሽ አስተውህሎት የበለፀገ ምሥል

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0