ኢትዮጵያዊቷ አትሌት ማርታ አለማየሁ በዓለም አትሌቲክስ የሀገር አቋራጭ ሻምፒዮና ተከታታይ ድል ያስመዘገበች አራተኛዋ አትሌት ሆነች

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱኢትዮጵያዊቷ አትሌት ማርታ አለማየሁ በዓለም አትሌቲክስ የሀገር አቋራጭ ሻምፒዮና ተከታታይ ድል ያስመዘገበች አራተኛዋ አትሌት ሆነች
ኢትዮጵያዊቷ አትሌት ማርታ አለማየሁ በዓለም አትሌቲክስ የሀገር አቋራጭ ሻምፒዮና ተከታታይ ድል ያስመዘገበች አራተኛዋ አትሌት ሆነች - Sputnik አፍሪካ, 1920, 11.01.2026
ሰብስክራይብ

ኢትዮጵያዊቷ አትሌት ማርታ አለማየሁ በዓለም አትሌቲክስ የሀገር አቋራጭ ሻምፒዮና ተከታታይ ድል ያስመዘገበች አራተኛዋ አትሌት ሆነች

አትሌቷ በአሜሪካ ፍሎሪዳ ግዛት ታላሃሲ ከተማ ትናንት ተካሄዶ በነበረው 46ኛው የዓለም አትሌቲክስ አገር አቋራጭ ሻምፒዮና፤ የ6 ኪሎ ሜትር የሴቶች ከ20 ዓመት በታች ውድድርን በ18 ደቂቃ ከ52 ሰከንድ በማሸነፍ የወርቅ ሜዳሊያ አግኝታለች።

በዚህም ከለተሰንበት ግደይ፣ ጄን ቼፕቲዩ (ኡጋንዳ) እና ፌይዝ ኪፕዬጎን (ኬንያ) በመቀጠል ውድድሩን በ2024 (ቤልግሬድ) እና በ2026 (ታላሃሲ) በተከታታይ በማሸነፍ የበላይነቷን ያስቀጠለች አራተኛዋ ሴት አትሌት በመሆን ታሪክ አስመዝግባለች።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0