የሃላባ ብሔረሰብ የዘመን መለወጫ "ሴራ" በዓልን እያከበረ ነው
15:16 11.01.2026 (የተሻሻለ: 15:24 11.01.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የሃላባ ብሔረሰብ የዘመን መለወጫ "ሴራ" በዓልን እያከበረ ነው
በዓሉን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለማስመዝገብ ጥናት እየተደረገ መሆኑም ተገልጿል፡፡
የሃላባ የዘመን መለወጫ "ሴራ" በዓል በባሕላዊ የዘመን አቆጣጠር ስርዓት በየዓመቱ ከታህሳስ መጨረሻ እስከ ጥር ወር መጀመሪያ ባሉ ቀናት ውስጥ ይከበራል።
በዕለቱ አባቶች የተጣሉ ሰዎችን በማስታረቅ በዓሉን በጋራ እንዲያከብሩ የሚያደርጉበት ማኅበራዊ ኃላፊነት የበዓሉ መገለጫ ነው።
የኢትዮጵያ ቅርስ ባለሥልጣን የ "ሴራ" በዓልን በዓለም አቀፍ ቅርስነት ለማስመዝገብ የሚያስችሉ ጥናታዊ ሥራዎችን እያከናወነ መሆኑን ኃላፊዎችን ጠቅሶ የሀገር ውስጥ ሚዲያ ዘግቧል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

