ቶጎ የአኩሪ አተር፣ የካሹ እና የሺዓ ምርቶችን በሀገር ውስጥ መቀነባበር ለማበረታታት የወጪ ንግድ ታክስ ጣለች
20:00 10.01.2026 (የተሻሻለ: 20:04 10.01.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ቶጎ የአኩሪ አተር፣ የካሹ እና የሺዓ ምርቶችን በሀገር ውስጥ መቀነባበር ለማበረታታት የወጪ ንግድ ታክስ ጣለች
እ.አ.አ ከጥር 1 ጀምሮ ተግባራዊ የተደረገው ይህ እርምጃ፤ የጥሬ ምርቶችን የወጪ ንግድ በመገደብ፤ በሀገር ውስጥ ተቀነባብረው ከፍተኛ ተጨማሪ እሴት እንዲፈጥሩ ለማድረግ ያለመ መሆኑን የአካባቢው መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል።
እርምጃው በተለይ የካሹ እና የሺዓ ለውዝ ምርቶችን ጨምሮ፤ ስትራቴጂያዊ የግብርና ዘርፎችን ለማነቃቃት በ2018 የተጀመሩ ሥራዎች አካል ነው።
በኪሎግራም ከ$0.0017 እስከ $0.17 የተቆረጠው የታሪፍ ተመን፤ የኢኮኖሚ አንቀሳቃሾች በማቀነባበሪያ ፋብሪካዎች ላይ ኢንቨስት እንዲያደርጉ ለማበረታታት ታስቦ የተዘጋጀ ነው።
ታክሱ ኢንዱስትሪንና የሥራ ዕድልን ከማጠናከር ባለፈ፤ የመንግሥትን የግብር ገቢ ለማብዛትና የቶጎን የኢኮኖሚ ሉዓላዊነት ለማረጋገጥ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ተብሏል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X