ኢትዮጵያና ኬንያ በ2026 የአፍሪካን የኢኮኖሚ ዕድገት እንደሚመሩ ተመድ አስታወቀ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱኢትዮጵያና ኬንያ በ2026 የአፍሪካን የኢኮኖሚ ዕድገት እንደሚመሩ ተመድ አስታወቀ
ኢትዮጵያና ኬንያ በ2026 የአፍሪካን የኢኮኖሚ ዕድገት እንደሚመሩ ተመድ አስታወቀ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 10.01.2026
ሰብስክራይብ

ኢትዮጵያና ኬንያ በ2026 የአፍሪካን የኢኮኖሚ ዕድገት እንደሚመሩ ተመድ አስታወቀ

በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የ2026 የዓለም ኢኮኖሚ ሁኔታ እና የትንበያ ሪፖርት መሠረት፤ ዘንድሮ የአፍሪካ ኢኮኖሚ 4 በመቶ ያድጋል ተብሎ ይጠበቃል።

ይህም ባለፉት ሁለት ዓመታት ከተመዘገቡት የ3.5 እና የ3.9 በመቶ ዕድገት የተሻለ ውጤት እንደሚሆን የተገለፀ ሲሆን ለዚህ ዕድገት ኢትዮጵያ እና ኬንያ በዋናነት ከፍተኛውን ድርሻ እንደሚይዙ ተመላክቷል።

በ2026 5.8 በመቶ ይደርሳል ተብሎ የሚጠበቀው የምስራቅ አፍሪካ ቀጣና ዕድገት ከአፍሪካ ከፍተኛው ሲሆን የኢትዮጵያ እና የኬንያ የኢኮኖሚ አፈጻጸም፣ የታዳሽ ኃይል መስፋፋት እና የቀጣናዊ ትስስር መጠናከር መነሻ እንደሚሆን ተጠቁሟል።

ከፍተኛ የዕዳ ጫና፣ የምግብ ዋጋ ንረት እና የአጎአ ስምምነት የሚያበቃበት ጊዜ መቃረብ ለአኅጉሪቱ ዘላቂ ልማት ስጋት እንደሆኑ ሪፖርቱ ጠቅሷል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0