ትራምፕ በክርስቲያኖች ላይ ይደርሳል ካሉት ስቃይ ጋር በተያያዘ በናይጄሪያ ተጨማሪ ጥቃቶች ሊሰነዘሩ እንደሚችሉ አስጠነቀቁ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱትራምፕ በክርስቲያኖች ላይ ይደርሳል ካሉት ስቃይ ጋር በተያያዘ በናይጄሪያ ተጨማሪ ጥቃቶች ሊሰነዘሩ እንደሚችሉ አስጠነቀቁ
ትራምፕ በክርስቲያኖች ላይ ይደርሳል ካሉት ስቃይ ጋር በተያያዘ በናይጄሪያ ተጨማሪ ጥቃቶች ሊሰነዘሩ እንደሚችሉ አስጠነቀቁ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 10.01.2026
ሰብስክራይብ

ትራምፕ በክርስቲያኖች ላይ ይደርሳል ካሉት ስቃይ ጋር በተያያዘ በናይጄሪያ ተጨማሪ ጥቃቶች ሊሰነዘሩ እንደሚችሉ አስጠነቀቁ

ባለፈው ታህሳስ ወር መጨረሻ የተሰነዘሩትን ጥቃቶች ተከትሎ፤ ትራምፕ እርምጃዎችን መውሰድ እንደሚቀጥሉ ፍንጭ ቢሰጡም ድርጊቱ የአንድ ጊዜ ብቻ ይሆናል ብለው ተስፋ እንደሚያደርጉ ገልጸዋል።

“ነገር ግን እነሱ [አሸባሪዎች] ክርስቲያኖችን መግደላቸውን የሚቀጥሉ ከሆነ ጥቃቱ በተደጋጋሚ የሚፈጸም ይሆናል” ሲሉ ለአንድ የአሜሪካ ጋዜጣ በሰጡት ቃለመጠይቅ ላይ ተናግረዋል።

ክርስቲያኖች ቀዳሚ ሰለባዎች ቢሆኑም በናይጄሪያ ሙስሊሞችም እንደሚገደሉ ትራምፕ ጠቅሰዋል።

የናይጄሪያ መንግሥት በሀገሪቱ “የክርስቲያን የዘር ማጥፋት ወንጀል” እየተፈጸመ ነው የሚሉ ክሶችን በተደጋጋሚ ውድቅ ማድረጉ ይታወሳል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0