የድሬ ሼኽ ሁሴን መስጂድን በዓለም ቅርስነት ለማስመዝገብ እና የቱሪስት መዳረሻ ለማድረግ እየተሠራ እንደሆነ ተገለፀ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱየድሬ ሼኽ ሁሴን መስጂድን በዓለም ቅርስነት ለማስመዝገብ እና የቱሪስት መዳረሻ ለማድረግ እየተሠራ እንደሆነ ተገለፀ
የድሬ ሼኽ ሁሴን መስጂድን በዓለም ቅርስነት ለማስመዝገብ እና የቱሪስት መዳረሻ ለማድረግ እየተሠራ እንደሆነ ተገለፀ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 10.01.2026
ሰብስክራይብ

የድሬ ሼኽ ሁሴን መስጂድን በዓለም ቅርስነት ለማስመዝገብ እና የቱሪስት መዳረሻ ለማድረግ እየተሠራ እንደሆነ ተገለፀ

በምስራቅ ባሌ ዞን የሚገኘውን ይህን ጥንታዊ፣ መንፈሳዊ እና ታሪካዊ ስፍራ በዓለም ቅርስነት ለማስመዝገብ ጥረት እየተደረገ መሆኑን የኢትዮጵያ ቅርስ ጥበቃ ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳሬክተር ሕይወት ኃይሉ ተናግረዋል።

የቅርሱን ገፅታ መቀየር የሚያስችል የመንገድ፣ የኤሌትሪክ ኃይል እና ንፁህ የመጠጥ ውሃ ተደራሽ ለማድረግ ተግባራዊ እንቅስቃሴ መጀመሩን የሀገር ውስጥ ሚዲያ የአካባቢውን ባለሥልጣን ጠቅሶ ዘግቧል።

የጥንታዊ ኢትዮጵያ የግንባታ ጥበብ ውጤት ማሳያ ነው የተባለው የድሬ ሼኽ ሁሴን መስጂድ፦

በ11ኛው ክፍለ ዘመን የተገነባ፣

የውሃ ኩሬን ጨምሮ በርካታ የጥንታዊ ስልጣኔ መገለጫዎች የሚገኙበት፤

በሙሉ ነጭ ቀለም ያሸበረቁ ሕንፃዎች ያሉት ነው።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0