የሕንዱ ሬልቴል ለኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አዲስ የመረጃ ማዕከል ሊገነባ ነው
13:25 10.01.2026 (የተሻሻለ: 13:34 10.01.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የሕንዱ ሬልቴል ለኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አዲስ የመረጃ ማዕከል ሊገነባ ነው
የሕንድ መንግሥት የቴክኖሎጂ ተቋም፤ የመረጃ ማዕከሉን ግንባታ በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ አጠናቆ ለማስረከብ የሚያስችለውን ውል የሕንድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እንደፈረመ አስታውቋል።
በተጨማሪም ተቋሙ ለተከታዮቹ ሦስት ዓመታት የጥገና እና የሥራ ማስኬጃ አገልግሎት ለመስጠት የተስማማ ሲሆን ይህም ማዕከሉ ያለ ምንም መቆራረጥ በዘላቂነት አገልግሎት እንዲሰጥ ዋስትና እንደሚሆን ተነግሯል።
ፕሮጀክቱ የ “ዲጂታል ኢትዮጵያ” ስትራቴጂን ለማሳካት እና የሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱን የመረጃ አያያዝ ሥርዓት ዘመናዊ ለማድረግ እንደሚያግዝ ተመላክቷል።
ዜናው የሕንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ በቅርቡ በኢትዮጵያ ባደረጉት ጉብኝት ሁለቱ ሀገራት በተለያዩ መስኮች ስምምነት መፈራረማቸውን ተከትሎ የመጣ ነው፡፡
በሰው ሠራሽ አስተውህሎት የበለፀገ ምሥል
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X