ማሊ የብሔራዊ እርቅ አካል የሆኑ 341 የቀድሞ አማፂያንን ወደ ጦር ሠራዊቱ ቀላቀለች

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱማሊ የብሔራዊ እርቅ አካል የሆኑ 341 የቀድሞ አማፂያንን ወደ ጦር ሠራዊቱ ቀላቀለች
ማሊ የብሔራዊ እርቅ አካል የሆኑ 341 የቀድሞ አማፂያንን ወደ ጦር ሠራዊቱ ቀላቀለች - Sputnik አፍሪካ, 1920, 09.01.2026
ሰብስክራይብ

ማሊ የብሔራዊ እርቅ አካል የሆኑ 341 የቀድሞ አማፂያንን ወደ ጦር ሠራዊቱ ቀላቀለች

በማሊ ቲምቡክቱ እና ታውዴኒት ክልሎች ትጥቅ የማስፈታት፣ የመበተን እና ወደ ማኅበረሰቡ የመቀላቀል ጥረት በይፋ መጀመሩን የማሊ ጦር ኃይሎች አስታውቋል።

የክልል ገዥዎች በተገኙበት እና የብሔራዊ ኮሚሽኑ ኃላፊዎች እንዲሁም የአካባቢው ባለሥልጣናት የተሳተፉበት የቲምቡክቱ ሥነ-ሥርዓት፤ ለሀገራዊ እርቅ ሂደቱ ትልቅ እርምጃ መሆኑን ጦሩ ገልጿል።

🪖 መርኃ-ግብሩ የማሊን ጦር ለማጠናከር፣ ሥራ አጥነትን ለመቀነስ እና የጦር መሣሪያ ዝውውርን ለመግታት ያለመ መሆኑ ተመላክቷል።

በዚህም 341 የቀድሞ ተዋጊዎች በሁለተኛ ደረጃ ወታደርነት ወደ ማሊ ጦር ይቀላቀላሉ። ባለሥልጣናት ሂደቱ ሁሉንም ያካተተ እና በማሊ ማኅበረሰብ እሴቶች፣ በዓለም አቀፍ የሰብዐዊ መብት ሕጎች እና በሰብዓዊ መብቶች ላይ የተመሠረተ መሆኑን ገልጸዋል።

በቲምቡክቱ የተከናወነው ምዕራፍ በሀገሪቱ ሲካሄዱ የቆዩ ተመሳሳይ ኦፕሬሽኖች ማጠቃለያ መሆኑን የማሊ ጦር አስታውቋል። ባለሥልጣናት ለዚህ ተነሳሽነት ስኬት የታጠቁ ቡድኖች መሪዎች እና የአካባቢው ማኅበረሰቦች ሙሉ ድጋፋቸውን እንዲሰጡ ጥሪ አቅርበዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱ
ማሊ የብሔራዊ እርቅ አካል የሆኑ 341 የቀድሞ አማፂያንን ወደ ጦር ሠራዊቱ ቀላቀለች - Sputnik አፍሪካ
1/2
© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱ
ማሊ የብሔራዊ እርቅ አካል የሆኑ 341 የቀድሞ አማፂያንን ወደ ጦር ሠራዊቱ ቀላቀለች - Sputnik አፍሪካ
2/2
1/2
2/2
አዳዲስ ዜናዎች
0