ከ20 በላይ የአረብ እና የእስልምና ሀገራት የእስራኤል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ወደ ሶማሊላንድ ያደረጉትን ያልተፈቀደ ጉብኝት አወገዙ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱከ20 በላይ የአረብ እና የእስልምና ሀገራት የእስራኤል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ወደ ሶማሊላንድ ያደረጉትን ያልተፈቀደ ጉብኝት አወገዙ
ከ20 በላይ የአረብ እና የእስልምና ሀገራት የእስራኤል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ወደ ሶማሊላንድ ያደረጉትን ያልተፈቀደ ጉብኝት አወገዙ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 09.01.2026
ሰብስክራይብ

ከ20 በላይ የአረብ እና የእስልምና ሀገራት የእስራኤል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ወደ ሶማሊላንድ ያደረጉትን ያልተፈቀደ ጉብኝት አወገዙ

የ23 ሀገራት ጥምረት የእስራኤል ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጊዲዮን ሳር ማክሰኞ ዕለት ወደ ራስ ገዟ ሶማሊላንድ ያደረጉትን ጉዞ አጥብቆ ማውገዙን የሶማሊያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል።

ይህ የጋራ መግለጫ የሳዑዲ አረቢያ፣ ግብፅ፣ ቱርክ፣ ኢራን፣ ፓኪስታን፣ ኳታር፣ ሱዳን እና ናይጄሪያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮችን ጨምሮ በሌሎች ሀገራት እንዲሁም በእስልምና ትብብር ድርጅት ድጋፍ የተሰጠው ነው።

ይህ ውግዘት እስራኤል በቅርቡ ሶማሊላንድን እንደ ነጻ ሉዓላዊ ሀገር እውቅና ለመስጠት የወሰደችውን አወዛጋቢ ውሳኔ ተከትሎ የመጣ ነው።

ዋና ዋና ተቃውሞዎች እና ጥሪዎች፦

🟠 የሉዓላዊነት ጥሰት፦ ጉብኝቱ የሶማሊያን የግዛት አንድነት "በግልጽ የሚጥስ"፣ ዓለም አቀፍ ደንቦችን እና የተባበሩት መንግሥታትን ቻርተር የሚጻረር መሆኑን ሚኒስትሮቹ ገልጸዋል።

🟠 ለመረጋጋት የሚፈጥረው ስጋት፦ የመገንጠል አጀንዳዎችን ማበረታታት ተቀባይነት የሌለው ተግባር መሆኑንና አስጊ በሆነው የአፍሪካ ቀንድ ቀጣና ውጥረት ሊያባብስ እንደሚችል አስጠንቅቀዋል።

🟠 እውቅናው እንዲነሳ የቀረበ ጥሪ፦ ጥምረቱ እስራኤል ለሶማሊላንድ የሰጠችውን እውቅና በአስቸኳይ እንድታነሳ፣ የሶማሊያን አንድነት ሙሉ በሙሉ እንድታከብር እና ለዓለም አቀፍ ሕግ ተገዢ እንድትሆን ጠይቋል።

ሀገራቱ ለሶማሊያ ሉዓላዊነት የማይናወጥ ድጋፋቸውን በድጋሚ በማረጋገጥ፤ ሞጋዲሹ ጉዳዩን በሰላማዊ ዲፕሎማሲ ለመፍታት ለምታደርገው ጥረት አድናቆታቸውን መግለጻቸውንም ሚኒስቴሩ አመልክቷል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0