የአልጄሪያ የፀረ-ቅኝ አገዛዝ ሕግ ሌሎች የአፍሪካ ሀገራትም ሊከተሉት የሚገባ ‘ደፋር ፖለቲካዊ እርምጃ’ ነው - የቡርኪናፋሶ ተንታኝ

ሰብስክራይብ

የአልጄሪያ የፀረ-ቅኝ አገዛዝ ሕግ ሌሎች የአፍሪካ ሀገራትም ሊከተሉት የሚገባ ‘ደፋር ፖለቲካዊ እርምጃ’ ነው - የቡርኪናፋሶ ተንታኝ

የአልጄሪያ ፓርላማ የፈረንሳይን የቅኝ ግዛት ዘመን ወንጀል አድርጎ ለመደንገግ በቅርቡ ያሳለፈው ውሳኔ፤ ከአፍሪካውያን ለረጅም ጊዜ ተሰርቆ የቆየውን ታሪካዊ እውነት ለመመለስ ያለመ መሆኑን ላቢዲ ናባ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።

የፖለቲካ ተንታኙ "ይህ የሕግ ውሳኔ ሌሎች የአፍሪካ ሀገራትም የአልጄሪያን አርአያነት በመከተል የጥቁር ሕዝቦችን ክብር ለመመለስና ለማረጋገጥ እንዲሁም በላያችን ላይ የተጫነውን የብዝበዛ ሥርዓት ለማውገዝ መሥራት እንዳለባቸው የሚያሳይ ነው" ብለዋል።

ይህ እርምጃ የአፍሪካን ወጣቶች የሚያነቃቃና ብዝበዛን ለማስቀጠል የታለሙ ማናቸውንም እቅዶች ሙሉ በሙሉ የሚያስቆም ነው ሲሉ ናባ አጽንዖት ሰጥተዋል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0