ኢትዮጵያ ዕሴት የታከለበትን ቡና በአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ገበያ ስር ማቅረብ ጀመረች
17:53 09.01.2026 (የተሻሻለ: 17:54 09.01.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ኢትዮጵያ ዕሴት የታከለበትን ቡና በአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ገበያ ስር ማቅረብ ጀመረች
ሀገሪቱ በአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጣና ሥምምነት መሠረት የቡና ገበያ መዳረሻዋን ለማስፋት እየሠራች እንደሆነ የኢትዮጵያ ቡና እና ሻይ ባለሥልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ሻፊ ዑመር ለሀገር ውስጥ ሚዲያ ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ የቡና ገበያ መዳረሻዎቿን በማስፋት በ2016 64 የነበረውን ቁጥር በ2017 ወደ 84 ማሳደግ መቻሏን ኃላፊው ተናግረዋል።
ነባር የቡና ገበያ መዳረሻዎችን በማጠናከር አዳዲስ ገበያዎችን ለማስፋት በተለያዩ ሀገራት ከሚገኙ የኢትዮጵያ ኤምባሲዎች ጋር በቅንጅት እየተሠራ እንደሚገኝም ገልፀዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X