ኢትዮጵያ ዕሴት የታከለበትን ቡና በአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ገበያ ስር ማቅረብ ጀመረች
17:53 09.01.2026 (የተሻሻለ: 17:54 09.01.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ኢትዮጵያ ዕሴት የታከለበትን ቡና በአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ገበያ ስር ማቅረብ ጀመረች
ሀገሪቱ በአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጣና ሥምምነት መሠረት የቡና ገበያ መዳረሻዋን ለማስፋት እየሠራች እንደሆነ የኢትዮጵያ ቡና እና ሻይ ባለሥልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ሻፊ ዑመር ለሀገር ውስጥ ሚዲያ ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ የቡና ገበያ መዳረሻዎቿን በማስፋት በ2016 64 የነበረውን ቁጥር በ2017 ወደ 84 ማሳደግ መቻሏን ኃላፊው ተናግረዋል።
ነባር የቡና ገበያ መዳረሻዎችን በማጠናከር አዳዲስ ገበያዎችን ለማስፋት በተለያዩ ሀገራት ከሚገኙ የኢትዮጵያ ኤምባሲዎች ጋር በቅንጅት እየተሠራ እንደሚገኝም ገልፀዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X