ኢትዮጵያ ባለፉት ስድስት ወራት ከ704 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቧን አስታወቀች
15:47 09.01.2026 (የተሻሻለ: 15:54 09.01.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ኢትዮጵያ ባለፉት ስድስት ወራት ከ704 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቧን አስታወቀች
በግማሽ ዓመቱ ከተሰበሰበው አጠቃላይ ገቢ ውስጥ 362.4 ቢሊዮን ብሩ ከሀገር ውስጥ ታክስ፤ ቀሪው 341.9 ቢሊዮን ብር ደግሞ ከወጪ ንግድ ቀረጥና ታክስ እንደተሰበሰበ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት አስታውቋል።
የተሰበሰበው ገቢ ከባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ63.7 ቢሊዮን ብር አብላጫ እንዳለውም ተጠቁሟል፡፡
ይህ አፈጻጸም ኢትዮጵያ በታሪኳ ከፍተኛውን የገቢ ግኝት ያስመዘገበችበት መሆኑን አገልግሎቱ በመግለጫው ጠቅሷል፡፡
በሀገር አቀፍ ደረጃ የተከናወኑ የኢኮኖሚ ማሻሽያዎች ለተገኝው ውጤት መነሻ መሆናቸውን ተቋሙ በመግለጫው አመላክቷል፡፡
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X