ሶማሊያ የምግብ እርዳታ ይዛለች የሚለውን የአሜሪካ ክስ በማስተባበል፣ የእርዳታ መቋረጡ በ"አለመግባባት" የተከሰተ መሆኑን ገለፀች
21:40 08.01.2026 (የተሻሻለ: 21:44 08.01.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ሶማሊያ የምግብ እርዳታ ይዛለች የሚለውን የአሜሪካ ክስ በማስተባበል፣ የእርዳታ መቋረጡ በ"አለመግባባት" የተከሰተ መሆኑን ገለፀች
የሶማሊያ መንግስት የሰብዓዊ እርዳታ ተቆጣጥራለች በሚል በአሜሪካ የቀረበበትን ውንጀላ ውድቅ ማድረጉን የሀገሪቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል። የዓለም የምግብ ፕሮግራም መጋዘን አሁንም ሙሉ በሙሉ በተባበሩት መንግስታት ቁጥጥር ስር መሆኑን ሚኒስቴሩ አረጋግጧል።
"ጥያቄ የተነሳበት የዓለም የምግብ ፕሮግራም መጋዘን የሚገኘው በሞቃዲሾ ወደብ ክልል ውስጥ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት በወደቡ ላይ የማስፋፊያ እና መልሶ የማደራጀት ስራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ" ሲል ሚኒስቴሩ በሰጠው ማብራሪያ ላይ ጠቁሟል። እነዚህ ስራዎች በእርዳታ ቁሳቁሶች አያያዝም ሆነ ስርጭት ላይ ምንም አይነት መስተጓጎል እንዳልፈጠሩም አክሏል።
የሶማሊያ መንግስት ጉዳዩን ከሰብዓዊ ድርጅቶች ጋር በመሆን በቴክኒክ ኮሚቴ አማካኝነት እየመረመረው መሆኑን ገልጾ፣ አሜሪካን ጨምሮ ለሁሉም ዓለም አቀፍ ለጋሾች ግልጽነት ባለው መንገድ ለመስራት ቁርጠኛ መሆኑን ሚኒስቴሩ በመግለጫው ጠቅሷል።
ይህ ምላሽ የተሰጠው የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ለሶማሊያ ፌዴራላዊ መንግስት የሚሰጠውን ማንኛውንም ዓይነት ድጋፍ ማቋረጡን ካስታወቀ በኋላ ነው። ዋሽንግተን በሰጠችው መግለጫ የሀገሪቱ ባለስልጣናት የዓለም የምግብ ፕሮግራም መጋዘንን አውድመዋል እንዲሁም 76 ቶን የሚመዝን የምግብ እርዳታ ለሌላ ዓላማ አውለዋል ስትል ከሳለች።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X