አሜሪካ በቬንዙዌላ ላይ የፈጸመችውን ጥቃትና የማዱሮን መታፈን በመቃወም በፕሪቶሪያ የአሜሪካ ኤምባሲ ፊት ለፊት ሰልፍ ተካሄደ

ሰብስክራይብ

አሜሪካ በቬንዙዌላ ላይ የፈጸመችውን ጥቃትና የማዱሮን መታፈን በመቃወም በፕሪቶሪያ የአሜሪካ ኤምባሲ ፊት ለፊት ሰልፍ ተካሄደ

የደቡብ አፍሪካ የንግድ ማኅበራት፣ የፖለቲካ ቡድኖች፣ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች እና የድጋፍ ሰጪ ንቅናቄዎች በዛሬው ዕለት ተሰባስበው አሜሪካ በሉዓላዊ ሀገራት የውስጥ ጉዳይ ጣልቃ መግባቷን ማውገዛቸው ተዘግቧል።

የብሪክስ ጋዜጠኞች ማሕበር ተባባሪ ሊቀ መንበር የሆኑት ኖንኩሉሌኮ ማንቱላ (ዶ/ር) በሰጡት መግለጫ፣ በኢምፔሪያሊስት ኃይሎች ተፅዕኖ ስር ካሉ ሀገራት ጋር አጋርነት መፍጠር አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል። ይህ አጋርነት ከቬንዙዌላ ጋር ብቻ ሳይሆን ከሩሲያ፣ ኢራን፣ ኢራቅ እና ሌሎች ሀገራት ጋርም መሆን እንዳለበት አጽንኦት ሰጥተዋል።

“ከታሳሪነት ተላቅቀን የራሳችንን ሀብት መጠቀም እንድንችል፣ እያንዳንዱ የሚዲያ ባለሙያ እውነትን እንዲናገርና ሀሰተኛ ትርክቶችን ከመቀበል እንዲቆጠብ እንፈልጋለን” ሲሉ ተናግረዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0