አሜሪካ በቬንዙዌላ ላይ የምታደርገው ቁጥጥር ከአንድ ዓመት ተሻግሮ "ለረዥም ግዜያት" ሊቀጥል ይችላል - ትራምፕ
19:25 08.01.2026 (የተሻሻለ: 19:34 08.01.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
አሜሪካ በቬንዙዌላ ላይ የምታደርገው ቁጥጥር ከአንድ ዓመት ተሻግሮ "ለረዥም ግዜያት" ሊቀጥል ይችላል - ትራምፕ
"ከአንድ ዓመት በጣም ለበለጠ ጊዜ" ሲሉ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አሜሪካ በነዳጅ የበለጸገችውን ቬንዙዌላን ለምን ያህል ጊዜ በቁጥጥሯ ስር እንደምታቆይ ከአንድ የአሜሪካ ጋዜጣ ለቀረበላቸው ጥያቄ ምላሽ ሰጥተዋል።
በተጨማሪም ትራምፕ ወደፊት ሁኔታዎች "አስተማማኝ ሲሆኑ" ቬንዙዌላን የመጎብኘት ፍላጎት እንዳላቸው ተናግረዋል።
አሜሪካ በቬንዙዌላ ላይ ቁጥጥር እያደረገች የአገሪቱን ነዳጅ የመጠቀም፣ የነዳጅ ዋጋን የመቀነስ እና ለካራካስ ገንዘብ የመስጠት እቅድ እንዳላት ፕሬዝዳንቱ ገልጸዋል።
"አገሪቱን በጣም ትርፋማ በሆነ መንገድ እንደገና እንገነባታለን... ነዳጁን እንጠቀምበታለን፤ እንወስደዋለን። የነዳጅ ዋጋን እንዲቀንስ እናደርጋለን፤ እንዲሁም ቬንዙዌላ በከፍተኛ ሁኔታ ለሚያስፈልጋት እርዳታ ገንዘብ እንሰጣለን" ብለዋል።
በተመሳሳይ፣ በካራካስ ላይ ወታደራዊ ዘመቻ በመክፈት የቬንዙዌላው ፕሬዝዳንት ኒኮላስ ማዱሮ በጥር 3 ቀን በቁጥጥር ስር እንዲውሉ ያደረጉት ትራምፕ፣ የአገሪቱን የነዳጅ ዘርፍ ወደ ቀድሞ ሁኔታው ለመመለስ ዓመታት ሊፈጅ እንደሚችል አምነዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X