ድርብ ደስታ - በምስራቅ ኮንጎ ብርቅዬ የተራራ ጎሪላ መንትዮች መወለዳቸው ተነገረ

ሰብስክራይብ

ድርብ ደስታ - በምስራቅ ኮንጎ ብርቅዬ የተራራ ጎሪላ መንትዮች መወለዳቸው ተነገረ

መንትያ ወንድ ጎሪላዎቹ ታኅሣሥ 25 ቀን በቪሩንጋ ብሔራዊ ፓርክ የታዩ ሲሆን፣ በጥሩ ጤንነት ላይ እንደሚገኙ የፓርኩ ባለሥልጣናት አስታውቀዋል። ይህ ክስተት ለአደጋ ለተጋለጠው ለዚህ ዝርያ ትልቅ ትርጉም ያለው ክስተት መሆኑን ገልጸዋል።

"ይህ የ2026 የመጀመሪያው ልደት የባገኒ ቤተሰብ አባላትን ቁጥር 59 በማድረስ በፓርኩ ውስጥ ትልቁ ያደርገዋል። በመንትዮቹ የመጀመሪያ ወሳኝ የዕድገት ወቅት ጤንነታቸውን ለመጠበቅ ተጨማሪ የክትትልና የጥበቃ እርምጃዎች ተወስደዋል" ሲል ፓርኩ በመግለጫው አስታውቋል።

መንትዮቹ የተወለዱት ማፉኮ ከተባለች የ22 ዓመት ጎሪላ ሲሆን፣ እናቷ እ.አ.አ በ2007 በታጠቁ ግለሰቦች ተገድላባት እንደነበር ተገልጿል። ማፉኮ ቀደም ሲል በ2016 መንትዮችን ወልዳ የነበረ ቢሆንም፣ ከአንድ ሳምንት በላይ መቆየት ሳይችሉ ሕይወታቸው አልፏል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0