በቡርኪና ፋሶ የመፈንቅለ መንግሥት ሴራ ከሸፈ - የቀድሞው መሪ ዳሚባ ዋና አቀናባሪ መሆናቸው ተገለጸ - ሚኒስትሩ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱበቡርኪና ፋሶ የመፈንቅለ መንግሥት ሴራ ከሸፈ - የቀድሞው መሪ ዳሚባ ዋና አቀናባሪ መሆናቸው ተገለጸ - ሚኒስትሩ
በቡርኪና ፋሶ የመፈንቅለ መንግሥት ሴራ ከሸፈ - የቀድሞው መሪ ዳሚባ ዋና አቀናባሪ መሆናቸው ተገለጸ - ሚኒስትሩ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 07.01.2026
ሰብስክራይብ

በቡርኪና ፋሶ የመፈንቅለ መንግሥት ሴራ ከሸፈ - የቀድሞው መሪ ዳሚባ ዋና አቀናባሪ መሆናቸው ተገለጸ - ሚኒስትሩ

​የቡርኪና ፋሶ የደህንነት ሚኒስትር ማሃማዱ ሳና በቴሌቪዥን በተላለፈ ቪዲዮ መልዕክት ላይ የሚከተሉትን ዝርዝሮች አጋርተዋል፡-

▪ በታኅሣሥ 25 ​"ሀገሪቱን የማተራመስ ሙከራው" ታቅዶ ነበር።

▪ ​አቀናባሪዎቹ ኢብራሂም ትራውሬን እና በርካታ ወታደራዊና ሲቪል ባለሥልጣናትን ለመግደል፣ "የድሮን ጣቢያን" ከጥቅም ውጪ ለማድረግ እና በመቀጠልም "በውጭ ኃይሎች የሚደረግ የመሬት ላይ ወታደራዊ ጣልቃገብነት" ለማድረግ አስበው ነበር።

▪ ​"ዋናው ተዋናይ" እ.ኤ.አ.በመስከረም 30, 2022 በኢብራሂም ትራኦሬ ከሥልጣን የተወገዱት እና በአሁኑ ጊዜ በቶጎ በግዞት የሚገኙት የቀድሞ የሽግግር ፕሬዝዳንት ፖል-ሄንሪ ሳንዳኦጎ ዳሚባ ናቸው።

▪ ​"አብዛኛው የገንዘብ ድጋፍ የመጣው ከኮት ዲቯር ሲሆን፣ የቅርቡ አስተዋፅዖ 70 ሚሊዮን እንደደረሰ ተዘግቧል።"

▪ ​ምርመራ እና አሰሳ እየተካሄደ ሲሆን በርካታ ሲቪሎችም ታስረዋል። ​ሁኔታው በአሁኑ ጊዜ ቁጥጥር ስር የዋለ ሲሆን ሁሉም ተሳታፊዎች "በፋሶ ዓቃቤ ሕግ ፊት ይቀርባሉ። የሕግ የበላይነትም ሙሉ በሙሉ ይተገበራል።"

​ ሚኒስትሩ "በምርመራ ላይ ያሉ ቁልፍ ግለሰቦች የእምነት ቃላቸውን የሚገልጹ ቪዲዮዎችን" ለመገናኛ ብዙኃን እንደሚለቁ ቃል ገብተዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0