የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን በጊኒ የተካሄደውን ምርጫ ውጤት ተቀበለ፤ ማዕቀቦች እንዲነሱም ሐሳብ አቀርቧል

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱየአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን በጊኒ የተካሄደውን ምርጫ ውጤት ተቀበለ፤ ማዕቀቦች እንዲነሱም ሐሳብ አቀርቧል
የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን በጊኒ የተካሄደውን ምርጫ ውጤት ተቀበለ፤ ማዕቀቦች እንዲነሱም ሐሳብ አቀርቧል - Sputnik አፍሪካ, 1920, 06.01.2026
ሰብስክራይብ

የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን በጊኒ የተካሄደውን ምርጫ ውጤት ተቀበለ፤ ማዕቀቦች እንዲነሱም ሐሳብ አቀርቧል

የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ባወጣው መግለጫ፤ "የኮሚሽኑ ሊቀመንበር ማሐሙድ አሊ ዩሱፍ፤ ለተመረጡት የጊኒ ሪፐብሊክ ፕሬዚዳንት ለተከበሩ ጄኔራል ማማዲ ዱምቡያ ሞቅ ያለ የእንኳን ደስ አለዎት መልዕክት አስተላልፈዋል" ብሏል።

ሊቀምንበሩ፤ ታኅሣሥ 19 የተካሄደውን ምርጫ "ሰላማዊና የተረጋጋ" እንዲሁም "ከዓለም አቀፍ መስፈርቶች እና ከሀገሪቱ የሕግ ማዕቀፍ ጋር በተጣጣመ መልኩ" የተከናወነ ሲሉ ገልጸውታል።

መግለጫው አክሎም፤ "እ.ኤ.አ ከ2021 የሽግግር ግዜ ጀምሮ የጊኒ ሪፐብሊክ ያስመዘገበችውን መሻሻል ግምት ውስጥ በማስገባት፤ የአፍሪካ ኅብረት እና ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ በሀገሪቱ ያለውን ሁኔታ በመገምገም በጊኒ ላይ የተጣሉ ማዕቀቦች የሚነሱበትን ሁኔታ እንዲያጤኑ ሊቀመንበሩ ያሳስባሉ" ብሏል።

እ.ኤ.አ 2021 በመፈንቅለ መንግሥት ወደ ሥልጣን የመጡት ጄኔራል ዱምቡያ፤ በምርጫው 86.72 በመቶ ድምፅ በማግኘት አሸንፈዋል። የሀገሪቱ ጠቅላይ ፍርድ ቤት እሁድ ዕለት በይፋ ፕሬዚዳንትነታቸውን አውጇል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0