በአፋር ክልል ሰመራ ከተማ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ22 ሰዎች ሕይወት አለፈ
16:15 06.01.2026 (የተሻሻለ: 16:24 06.01.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
በአፋር ክልል ሰመራ ከተማ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ22 ሰዎች ሕይወት አለፈ
አደጋው የተከሰተው ንጋት 11፡00 ሰዓት አካባቢ በሕገ-ወጥ ደላሎች ተታልለው ወደ ውጭ ሀገራት ለማቅናት የተሰባሰቡ ዜጎችን አጭቆ ሲጓዝ የነበረ ተሳቢ ተሽከርካሪ በሰመራ ከተማ አደባባይ ላይ በመገልበጡ እንደሆነ የአፋር ክልል የኮሚኒኬሽን ቢሮ አስታውቋል፡፡
በደረሰው አደጋ እስካሁን የ22 ሰዎች ሕይወት ማለፉ የተረጋገጠ ሲሆን የሟቾች ቁጥርም ከጉዳቱ ስፋት አንጻር ሊያሻቅብ እንደሚችል ተገልጿል፡፡
በአደጋው 30 ሰዎች ላይ ከባድ እንዲሁም 35 ሰዎች ላይ ቀላል የአካል ጉዳት የደረሰ ሲሆን በአጠቃላይ 65 ተጎጂዎች በዱብቲ ሪፈራል ሆስፒታል የሕክምና ክትትል እየተደረገላቸው እንደሚገኝ የአፋር ክልል የኮሙኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ መሐመድ አሊ ቢኢዶ ተናግረዋል፡፡
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

