ፎስቲን አርካንጅ ቱዋዴራ የማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ አሸናፊ መሆናቸው ታወጀ
12:51 06.01.2026 (የተሻሻለ: 12:54 06.01.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ፎስቲን አርካንጅ ቱዋዴራ የማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ አሸናፊ መሆናቸው ታወጀ
ቱዋዴራ ታኅሣሥ 19 የተካሄደውን ምርጫ 76.15 በመቶ ድምፅ በማግኘት ለሦስተኛ ጊዜ እንደተመረጡ የሀገሪቱ ብሔራዊ የምርጫ ባለሥልጣን አስታውቋል።
◻ ዋና ተቀናቃኛቸው አኒሴ ጆርጅ ዶሎግሌ በ14.66 በመቶ ድምፅ ሁለተኛ ደረጃን ሲይዙ፤ ሄንሪ ማሪ ዶንድራ ደግሞ 3.19 በመቶ አግኝተዋል።
◻ በተመሳሳይ ቀን በተካሄዱት የፕሬዚዳንታዊ፣ የሕግ አውጪ፣ የክልላዊ እና ማዘጋጃ ቤት ምርጫዎች የመራጮች ተሳትፎ 52.43 በመቶ ነበር።
◻ የምርጫ ባለሥልጣኑ አኃዝ ጊዜያዊ ሲሆን የመጨረሻው ውጤት በጥር ወር መጨረሻ ላይ በሕገ-መንግሥታዊ ምክር ቤት ይፋ ይደረጋል።
ፎስቲን አርካንጅ ቱዋዴራ ለመጀመሪያ ጊዜ እ.ኤ.አ በ2016፤ በ2020 ደግሞ ለሁለተኛ ጊዜ በድጋሚ ተመርጠዋል፡፡
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X