በአሜሪካ የቬንዙዌላ ጥቃት ዙሪያ እስካሁን የታወቁ መረጃዎች

በአሜሪካ የቬንዙዌላ ጥቃት ዙሪያ እስካሁን የታወቁ መረጃዎች
🟠 አሜሪካ የቬንዙዌላን የወደፊት ዕጣ ፈንታ በመወሰን ረገድ ተሳትፎ እንደምታደርግ ትራምፕ አስታውቀዋል።
🟠 ማዱሮ እና ባለቤታቸው በሄሊኮፕተር ከቬንዙዌላ እንዲወጡ ተደርገው ወደ ኒው ዮርክ በሚወስዳቸው መርከብ ላይ መሳፈራቸውን ትራምፕ ተናግረዋል።
🟠 የቬንዙዌላው ፕሬዚዳንት በአሜሪካ ፍርድ ቤት ቀርበው የወንጀል ክስ እንደሚመሰረትባቸው ሴናተር ማይክ ሊ፤ ሩቢዮን ዋቢ በማድረግ ይፋ አድርገዋል።
🟠 ቬንዙዌላ መብቷን በሁሉም ዓለም አቀፍ መድረኮች እንደምትከላከል እና ለዚህም ያሉትን ሁሉንም አማራጮች እንደምትጠቀም የሀገሪቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል።
🟠 አሜሪካ በቬንዙዌላ ላይ በሰነዘረችው ጥቃት ወታደራዊ አባላት እና ሲቪሎች መገደላቸውን ምክትል ፕሬዚዳንት ዴልሲ ሮድሪጌዝ ገልጸዋል።
🟠 የሩሲያው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌ ላቭሮቭ፤ ከዴልሲ ሮድሪጌዝ ጋር በስልክ ባደረጉት ውይይት፤ የጥቃት ወረራ ለተቃጣበት የቬንዙዌላ ሕዝብ ያላቸውን አብሮነት መግለጻቸውን የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል።
🟠 ነዋሪዎች የአሜሪካን ጥቃት ለመቃወም እና ለፕሬዚዳንት ማዱሮ ድጋፋቸውን ለመግለጽ በቬንዙዌላ አደባባዮች ወጥተዋል።
🟠 አሜሪካ ለሁለተኛ ዙር ጥቃት ዝግጁ የነበረች ቢሆንም ጥቃቱ ግን አስፈላጊ ሆኖ እንዳልተገኘ ትራምፕ ተናግረዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X