በቬንዙዌላ ላይ የተሰነዘረው ወታደራዊ እርምጃ “ፍጹም ሕገ-ወጥ እና ምንም ዓይነት ምክንያት የሌለው ቅይጥ ጥቃት ነው” - ተንታኝ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱበቬንዙዌላ ላይ የተሰነዘረው ወታደራዊ እርምጃ “ፍጹም ሕገ-ወጥ እና ምንም ዓይነት ምክንያት የሌለው ቅይጥ ጥቃት ነው” - ተንታኝ
በቬንዙዌላ ላይ የተሰነዘረው ወታደራዊ እርምጃ “ፍጹም ሕገ-ወጥ እና ምንም ዓይነት ምክንያት የሌለው ቅይጥ ጥቃት ነው” - ተንታኝ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 03.01.2026
ሰብስክራይብ

በቬንዙዌላ ላይ የተሰነዘረው ወታደራዊ እርምጃ “ፍጹም ሕገ-ወጥ እና ምንም ዓይነት ምክንያት የሌለው ቅይጥ ጥቃት ነው” - ተንታኝ

"ይህ ጥቃት ኮማንደር ሁጎ ቻቬዝ እና ፕሬዚዳንት ኒኮላስ ማዱሮ በቬንዙዌላ ላይ ስላለው የአሜሪካ ጣልቃ ገብነት፣ ስለ ኢኮኖሚ ጦርነቱ፣ ስለ ማዕቀቦቹ እና ስለ ቬንዙዌላ ሕዝብ ስቃይ ለዓመታት ሲናገሩ የነበረውን ሁሉ የሚያረጋግጥ ነው" ሲሉ አርጀንቲናዊው የዓለም አቀፍ ግንኙነት ባለሙያ ታዴዎ ካስቴግሊዮን ለስፑትኒክ ተናግረዋል።

በቬንዙዌላ ላይ የታየው ወታደራዊ ውጥረት እንደ አርጀንቲና እና ሆንዱራስ ባሉ የላቲን አሜሪካ ሀገራት ምርጫዎች ላይ የታየውን የአሜሪካ ጣልቃ ገብነት ዘይቤ የሚከተል መሆኑን ተንታኙ ጠቁመዋል።

አክለውም ጥቃቱ “ምንም ዓይነት ሕግ የማይከበርበት፣ ፍጹም ቁጥጥር የሌለበት እና አሜሪካ፤ በአሜሪካ አህጉር ጉዳዮች ላይ በሙሉ ኃይል ጣልቃ የምትገባበት ዓመት ውስጥ መግባታችንን ያሳያል” ብለዋል።

"ይህ ሁኔታ የአሜሪካ መንግሥት አደገኛና ፍጹም ምክንያታዊ ያልሆነ ደረጃ ላይ መድረሱን ያሳያል" ሲሉ ካስቴግሊዮን ደምድመዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0