ማሊ በባማኮ የኤሌክትሪክ አገልግሎት ለማረጋገጥ የ64 ሚሊዮን ዶላር የገንዘብ ድጋፍ ስምምነት አጸደቀች
19:21 02.01.2026 (የተሻሻለ: 19:24 02.01.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ማሊ በባማኮ የኤሌክትሪክ አገልግሎት ለማረጋገጥ የ64 ሚሊዮን ዶላር የገንዘብ ድጋፍ ስምምነት አጸደቀች
በእስልምና ልማት ባንክ የቀረበው ይህ የገንዘብ ድጋፍ “ሰሜናዊ ቀለበት” ተብሎ የሚጠራውን የ225 ኪሎ ቮልት የኃይል መሠረተ ልማት ለመገንባት የሚውል ነው። ፕሮጀክቱ የዋና ከተማዋን የኤሌክትሪክ ማሠራጫ በማጠናከር የኃይል አቅርቦት ለማረጋጋት ታስቦ የተነደፈ እንደሆነ ተገልጿል።
የፕሮጀክቱ ዋና ዓላማዎች፦
◻ የመሠረተ ልማት አውታሮችን በማዘመን የኃይል መቆራረጥን እና ቴክኒካዊ ብክነትን መቀነስ፣
◻ ከሴኔጋል ወንዝ ተፋሰስ ልማት ባለሥልጣን እና ከቀጣናዊ ትስስር የሚገኘውን ተወዳዳሪ የኃይል ምንጭ ማቀናጀት።
ይህ የኃይል ቀለበት ለማሊ የኢነርጂ ሉዓላዊነት ስትራቴጂ እንደ ዋነኛ ምሰሶ የሚታይ ነው። ለመኖሪያ ቤቶች እና ለንግድ ተቋማት ይበልጥ የተረጋጋ እና ዝቅተኛ ዋጋ ያለው የኤሌክትሪክ ኃይል በማከፋፈል የሀገሪቱን መንግሥት ቅድሚያ አጀንዳ የሚቀርፍ ይሆናል።
የማሊ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ስምምነቱን ማጽደቁን ተከትሎ ፕሮጀክቱ አሁን ወደ ትግበራ ምዕራፍ ተሸጋግሯል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X