ከሕዝብ ወደ 1.5 ቢሊዮን ያህል ብር በመሰብሰብ “ያጭበረበሩ” ቤት አልሚዎች በክስ ሂደት ላይ መሆናቸው ተገለፀ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱከሕዝብ ወደ 1
ከሕዝብ ወደ 1 - Sputnik አፍሪካ, 1920, 02.01.2026
ሰብስክራይብ

ከሕዝብ ወደ 1.5 ቢሊዮን ያህል ብር በመሰብሰብ “ያጭበረበሩ” ቤት አልሚዎች በክስ ሂደት ላይ መሆናቸው ተገለፀ

በ2017 በጀት ዓመት፤ “የቤት ባለቤት እናደርጋችኋለን” በሚል “በሰፊው የማጭበርበር ሥራ ላይ የተሰማሩ” ቤት አልሚ ተቋማት እና ግለሰቦች ላይ ሕጋዊ እርምጃ እየተወሰደ እንደሚገኝ የፍትሕ ሚኒስትር ሃና አርዓያሥላሴ ተናግረዋል፡፡

ሚኒስትሯ ይህን ያሉት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባካሄደው 7ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ በሕዝብ ስም የሚፈጸሙ የተለያዩ ወንጀሎችን በመመከላከል፣ ጥፋተኞችን በሕግ ተጠያቂ ከማድረግ አንጻር ከምክር ቤት አባላት ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ በሰጡበት ወቅት ነው።

“ከሕዝብ ንብረት ሰብስበው ከዳር ሳያደርሱ የሚሰወሩ እና የሚጠፉ አካላት ላይ የወንጀል ተጠያቂነትን እያሰፈንን እንገኛለን” ብለዋል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0