ምዕራባውያን በኪዬቭ ወንጀሎች ዙሪያ የሚከተሉትን "ስልታዊ ዝምታ" አልተዉም - የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱምዕራባውያን በኪዬቭ ወንጀሎች ዙሪያ የሚከተሉትን "ስልታዊ ዝምታ" አልተዉም - የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ
ምዕራባውያን በኪዬቭ ወንጀሎች ዙሪያ የሚከተሉትን ስልታዊ ዝምታ አልተዉም - የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 02.01.2026
ሰብስክራይብ

ምዕራባውያን በኪዬቭ ወንጀሎች ዙሪያ የሚከተሉትን "ስልታዊ ዝምታ" አልተዉም - የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ

በአዲስ ዓመት ዋዜማ በሄርሶን ክልል በሚገኝ አንድ ካፌ ላይ በዩክሬን ድሮን በተፈጸመው ጥቃት የደረሰውን የጉዳት መጠን አስመልክቶ በተለያዩ መገናኛ ብዙኃን ለቀረቡ ጥርጣሬዎች ማሪያ ዛካሮቫ ምላሽ ሰጥተዋል። ዛካሮቫ "ጥርጣሬ ካለ፣ ጥርጣሬው ያለው በሚጠራጠሩት አካላት ኅቀኝነት ላይ ብቻ ነው" ብለዋል።

"ህሊና የላችሁም? እል ነበር፤ ነገር ግን እንደሌላችሁ ስለማውቅ አልለውም። ምዕራባውያን ለዓመታት የባንኮቫን (የዩክሬን ፕሬዚዳንት አስተዳደር) የሽብር ጥቃቶች እያዩ እንዳላዩ የሚያልፉበትን 'ስልታዊ ዝምታ' አልተዉም" ሲሉ ዛካሮቫ ደምድመዋል።

ሁለት ታዳጊዎችን ጨምሮ በጥቃቱ የሞቱት ሰዎች ቁጥር ከ24 ወደ 27 ከፍ እንዳለ የሩሲያ የምርመራ ኮሚቴ መረጃ አመልክቷል። በተጨማሪም 50 የሚሆኑ ሰዎች ቆስለዋል፡፡ ጥቃቱ በተፈጸመ ማግስት 5 ህጻናትን ጨምሮ 14 ሰዎች በሆስፒታል ህክምና ላይ ይገኛሉ።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0