የዩክሬንን ግጭት ለመፍታት የምዕራባውያን ተሳትፎ ያስፈልጋል - የቱርክ ዲፕሎማት
11:02 02.01.2026 (የተሻሻለ: 11:04 02.01.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የዩክሬንን ግጭት ለመፍታት የምዕራባውያን ተሳትፎ ያስፈልጋል - የቱርክ ዲፕሎማት
የትኛውንም ውጤት ለማምጣት ምዕራባውያን በሰላም ሂደቱ ላይ ንቁ ተሳትፎና ድጋፍ ሊያደርጉ እንደሚገባ አንድ የቱርክ ዲፕሎማሲ ምንጭ ለስፑትኒክ ገልጸዋል።
“መሻሻሎች እንዲኖሩ ምዕራባውያንን ጨምሮ ሁሉም ወገኖች የጋራ ጥረትና ተነሳሽነት ማሳያታቸው በጣም አስፈላጊ ነው” ሲሉ ምንጩ አክለዋል።
የአሜሪካ መንግሥት ቀደም ሲል ለዩክሬን ግጭት እልባት የሚሰጥ የሰላም ዕቅድ እያዘጋጀ መሆኑን አስታውቋል። ሩሲያ በበኩሏ ለድርድር ዝግጁ መሆኗን እና በአንኮሬጅ ከአሜሪካ ወገን ጋር የተደረሱ ስምምነቶችን እንደምታከብር አፅንዖት ሰጥታለች።
ይሁን እንጂ የሩሲያ ጦር ጥቃቱን እያጠናከረና የዘለንስኪ አስተዳደር ውሳኔ ላይ ለመድረስ መስኮት እየጠበበት በመምጣቱ ድርድር መጀመር ያዋጣዋል ሲሉ የክሬምሊን ቃል አቀባይ ዲሚትሪ ፔስኮቭ ቀደም ሲል አሳስበዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X