የዩክሬንን ግጭት ለመፍታት የምዕራባውያን ተሳትፎ ያስፈልጋል - የቱርክ ዲፕሎማት

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱየዩክሬንን ግጭት ለመፍታት የምዕራባውያን ተሳትፎ ያስፈልጋል - የቱርክ ዲፕሎማት
የዩክሬንን ግጭት ለመፍታት የምዕራባውያን ተሳትፎ ያስፈልጋል - የቱርክ ዲፕሎማት - Sputnik አፍሪካ, 1920, 02.01.2026
ሰብስክራይብ

የዩክሬንን ግጭት ለመፍታት የምዕራባውያን ተሳትፎ ያስፈልጋል - የቱርክ ዲፕሎማት

የትኛውንም ውጤት ለማምጣት ምዕራባውያን በሰላም ሂደቱ ላይ ንቁ ተሳትፎና ድጋፍ ሊያደርጉ እንደሚገባ አንድ የቱርክ ዲፕሎማሲ ምንጭ ለስፑትኒክ ገልጸዋል።

“መሻሻሎች እንዲኖሩ ምዕራባውያንን ጨምሮ ሁሉም ወገኖች የጋራ ጥረትና ተነሳሽነት ማሳያታቸው በጣም አስፈላጊ ነው” ሲሉ ምንጩ አክለዋል።

የአሜሪካ መንግሥት ቀደም ሲል ለዩክሬን ግጭት እልባት የሚሰጥ የሰላም ዕቅድ እያዘጋጀ መሆኑን አስታውቋል። ሩሲያ በበኩሏ ለድርድር ዝግጁ መሆኗን እና በአንኮሬጅ ከአሜሪካ ወገን ጋር የተደረሱ ስምምነቶችን እንደምታከብር አፅንዖት ሰጥታለች።

ይሁን እንጂ የሩሲያ ጦር ጥቃቱን እያጠናከረና የዘለንስኪ አስተዳደር ውሳኔ ላይ ለመድረስ መስኮት እየጠበበት በመምጣቱ ድርድር መጀመር ያዋጣዋል ሲሉ የክሬምሊን ቃል አቀባይ ዲሚትሪ ፔስኮቭ ቀደም ሲል አሳስበዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0