ጋቦን አዲስ መንግሥት አቋቋመች
የጋቦን ፕሬዚዳንት የሀገሪቱ የሽግግር ጊዜ በተጠናቀቀ በሁለተኛው ቀን አዲስ የመንግሥት ስብጥር በትናንትናው ዕለት ይፋ አድርገዋል።
◻ 31 አባላትን ባቀፈው አዲሱ መንግሥት ርዕሰ ብሔሩ የሀገሪቱ መሪም ሆነው ያገለግላሉ።
◻ የመንግሥት ምስረታው ባለፈው ጥቅምት እና ህዳር ወር የተደረጉትን የሕግ መወሰኛ ምክር ቤት እና የአካባቢ ምርጫዎች ተከትሎ የመጣ ነው።
◻ አዲሱ አስተዳደር የመንግሥት ምክትል ፕሬዚዳንት እና የሪፐብሊኩ ምክትል ፕሬዚዳንትን ያካተተ ሲሆን በርካታ አዳዲስ ሚኒስትሮችም ተሹመዋል።
◻ ቀደም ሲል የሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስትር የነበሩት ሄርማን ኢሞንጋልት፤ የመንግሥት ሥራዎችን እንዲያስተባብሩ የመንግሥት ምክትል ፕሬዚዳንት ሆነው ተሹመዋል።
◻ የምክትል ፕሬዚዳንትነት ሥልጣን የጠቅላይ ሚኒስትርነትን ቦታ በመተካት በአምስተኛው ሪፐብሊክ ሕገ-መንግሥት ሥር የተዋወቀ ነው።
በሰው ሠራሽ አስተውህሎት የበለፀገ ምሥል
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
