ከፍተኛ የሩሲያ ባለሥልጣናት በሄርሶን ሆቴል ላይ የተፈጸመውን ጥቃት አወገዙ

ሰብስክራይብ

ከፍተኛ የሩሲያ ባለሥልጣናት በሄርሶን ሆቴል ላይ የተፈጸመውን ጥቃት አወገዙ

የሩሲያ ፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ ቫለንቲና ማትቪየንኮ፤ ሩሲያ በሄርሶን ክልል ንጹሃን ዜጎች ላይ የተፈጸመውን ጥቃት በተመለከተ ከዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ እና ከዓለም መሪዎች ውግዘት ትጠብቃለች ብለዋል።

“እየተመለከትን ያለነው ግልጽ የሆነ የሞራል ውድቀት ነው፤ ምንም ዓይነት የፖለቲካ ህይወት ሊኖራቸው አይገባም” ሲሉ አጽንኦት ሰጥተዋል።

ማትቪየንኮ በጥቃቱ የተጎዱትን ለመርዳት አስፈላጊውን ሁሉ እንደሚያደርጉም ገልጸዋል።

የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አምባሳደር ሮዲዮን ሚሮሽኒክ የማትቪየንኮን ንግግር በማጠናከር፤ የዩክሬን ኃይሎች በንጹሃን ዜጎች ላይ የፈጸሙት ግድያ ያለ ቅጣት ሊታለፍ አይገባም ብለዋል።

"ይህ ሰብዓዊነት የጎደለው ድርጊት ከዓለም ጠንካራ የሕግ እና የፖለቲካ ፍርድ ሊሰጠው ይገባል" ሲሉ አሳስበዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0