የአገው ፈረስ ባሕልን በዩኔስኮ የሰው ልጆች ወካይ ቅርስነት ለማስመዝገብ ቅድመ ሥራዎች መጠናቀቃቸው ተገለፀ
16:22 01.01.2026 (የተሻሻለ: 16:24 01.01.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የአገው ፈረስ ባሕልን በዩኔስኮ የሰው ልጆች ወካይ ቅርስነት ለማስመዝገብ ቅድመ ሥራዎች መጠናቀቃቸው ተገለፀ
ባሕላዊ ቅርሱ ዓለም አቀፍ እውቅና ማግኘት እንዲችል አስፈላጊ ሥራዎች ሲሠራ መቆየቱን እና በቀጣይ እውን ወደ ማድረግ እንደሚሸጋገር የአማራ ክልል የከተማ ልማት ዘርፍ አሥተባባሪ አሕመዲን ሙሐመድ (ዶ/ር) ተናግረዋል፡፡
የአገው ፈረስ ባሕል በተባበሩት መንግሥታት የትምህርት፣ የሳይንስና የባሕል ድርጅት መመዝገቡ የማኅበረሰቡን ተሳትፎ እና ማኅበራዊ መስተጋብር በማጎልበት በኩል አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ተጠቁሟል።
86ኛው የአገው ፈረሰኞች ዓመታዊ በዓል በመጪው ጥር ወር ይከበራል፡፡
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X