#viral| በአምስተርዳም 150 ዓመታትን ያስቆጠረ ታሪካዊ ቤተ-ክርስቲያን በእሳት ወደመ
16:02 01.01.2026 (የተሻሻለ: 16:04 01.01.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
#viral| በአምስተርዳም 150 ዓመታትን ያስቆጠረ ታሪካዊ ቤተ-ክርስቲያን በእሳት ወደመ
በኔዘርላንድስ ዋና ከተማ ማዕከል የሚገኘው እና በ "ኒዮ-ጎቲክ" የህንፃ ጥበብ ዘይቤ የታነጸው የቮንደልከርክ ቤተ-ክርስቲያን ህንፃ በደረሰበት ከባድ ቃጠሎ መውደሙን የአካባቢው መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል።
የታሪክ መታሰቢያ የሆነው ይህ ህንፃ ወደነበረበት ለመመለስ በማይቻል መልኩ ሙሉ በሙሉ መውደሙ ተነግሯል።
ሐሙስ ማለዳውን የተነሳው እሳት በፍጥነት ወደ ህንፃው አጠቃላይ መዋቅር ተሠራጭቷል። ህንፃው የመናድ አደጋ ስለተደቀነበት በደርዘን የሚቆጠሩ ነዋሪዎች ለጥንቃቄ ሲባል ከአካባቢው እንዲለቁ ተደርጓል።
በፒየር ኩይፐርስ የተነደፈው ቮንደልከርክ፤ የኔዘርላንድስ የባሕል ቅርስ አካል ሲሆን በቅርቡ የባሕል እና የማኅበረሰብ አገልግሎት መስጫ ማዕከል ሆኖ ሲያገለግል ቆይቷል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X