በ2018 በጀት ዓመት 600 ሺህ ቶን የቡና ምርት ለዓለም አቀፍ ገበያ እንደሚቀርብ የግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ
16:59 31.12.2025 (የተሻሻለ: 17:04 31.12.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
በ2018 በጀት ዓመት 600 ሺህ ቶን የቡና ምርት ለዓለም አቀፍ ገበያ እንደሚቀርብ የግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ
ለወጪ ንግድ ከሚቀርበው የቡና ምርት 3 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር ለማግኘት "እየተሠራ ነው" ሲሉ የግብርና ሚኒስትር አዲሱ አረጋ ተናግረዋል።
ባለፉት አምስት ወራት 174 ሺህ ቶን ቡና ወደ ውጪ በመላክ 1.2 ቢሊየን የአሜሪካ ዶላር ማግኘት መቻሉንም አስታውቀዋል።
ሚኒስትሩ ከ175 ሺህ ሄክታር በላይ ማሳን በቡና እያለማ የሚገኘውን የሲዳማ ክልል በጎበኙበት ወቅት ክልሉ በቀጣይ 40 ሺህ ቶን ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ለማቅረብ እየሠራ መሆኑ ተጠቁሟል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X