የጊኒ የሽግግር መንግሥት መሪ ማማዲ ዱምቡያ በፕሬዚዳንታዊ ምርጫው ማሸነፋቸው ተገለፀ
15:10 31.12.2025 (የተሻሻለ: 15:14 31.12.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የጊኒ የሽግግር መንግሥት መሪ ማማዲ ዱምቡያ በፕሬዚዳንታዊ ምርጫው ማሸነፋቸው ተገለፀ
የጊኒ የምርጫ ዳይሬክቶሬት ጄኔራል ባወጣው ጊዜያዊ ውጤት መሠረት፤ ማማዲ ዱምቡያ በፕሬዚዳንታዊ ምርጫው 86.72 በመቶ ድምፅ በማግኘት አሸንፈዋል።
የሀገሪቱ ጠቅላይ ፍርድ ቤት የምርጫውን ውጤት አስመልክቶ የሚቀርቡ ሕጋዊ ቅሬታዎች ካሉ ተመልክቶ፤ በስምንት ቀናት ውስጥ የዱምቡያን ድል እንደሚያፀድቅ ተገልጿል።
በግምት 85 በመቶ የሚሆን የመራጮች ተሳትፎ የታየበት ይህ ምርጫ፤ እ.ኤ.አ በ2021 ከተካሄደው ወታደራዊ መፈንቅለ መንግሥት በኋላ ሀገሪቱ ወደ ሲቪል አስተዳደር ሽግግር ማድረጓን የሚያበስር ይሆናል ተብሏል።
የመንግሥት ለውጡን የመሩት ዱምቡያ፤ በምርጫው ከሌሎች ስምንት ዕጩዎች ጋር የተወዳደሩ ሲሆን ድሉ ለሚቀጥሉት ሰባት ዓመታት ሀገሪቱን መመራት የሚያስችል ሥልጣን ይሰጣቸዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X