ቡናን ለምግብና መጠጥ ቱሪዝም ልማት ለመጠቀም እየሠራ መሆኑን የቱሪዝም ሚኒስቴር አስታወቀ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱቡናን ለምግብና መጠጥ ቱሪዝም ልማት ለመጠቀም እየሠራ መሆኑን የቱሪዝም ሚኒስቴር አስታወቀ
ቡናን ለምግብና መጠጥ ቱሪዝም ልማት ለመጠቀም እየሠራ መሆኑን የቱሪዝም ሚኒስቴር አስታወቀ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 31.12.2025
ሰብስክራይብ

ቡናን ለምግብና መጠጥ ቱሪዝም ልማት ለመጠቀም እየሠራ መሆኑን የቱሪዝም ሚኒስቴር አስታወቀ

የቡናን ታሪክና እሴት ከባሕላዊ ቱሪዝም ጋር በማቀናጀት የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ ገጽታ ለመገንባትና የውጭ ሀገር ጎብኚዎችን በመሳብ ዘርፉን ለመጠቀም ማለሙን ሚኒስቴሩ አስታውቋል፡፡

ዓለም አቀፍ ጎብኚዎች የቡናን ባሕል በተግባር የሚመለከቱበትን ዕድል በማመቻቸት የቱሪዝም ዘርፉን አማራጮች ለማስፋት በቅንጅት እየተሠራ እንደሚገኝ ተገልጿል።

ጎብኚዎች ከቡና ሥነ-ሥርዓት ባለፈ የቡና ለቀማና የደን ምርት አሰባሰብ ሂደት ላይ እንዲሳተፉ እንደሚደረግም ተጠቁሟል።

የቡና ምርት በሰፊ የሚገኝባቸው እንደ ይርጋለም፣ ይርጋጨፌ፣ ጅማ እና ከፋ ያሉ አካባቢዎች ለዚህ የቱሪዝም ዘርፍ በዋነኛነት ተለይተዋል ሲል የዘገበው የሀገር ውስጥ ሚዲያ ነው።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0