የትራምፕ እና የዘለንስኪ ውይይት አሜሪካ ለአላስካው ጉባኤ ያላትን ቁርጠኝነት ያሳያል – ወታደራዊ ተንታኝ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱየትራምፕ እና የዘለንስኪ ውይይት አሜሪካ ለአላስካው ጉባኤ ያላትን ቁርጠኝነት ያሳያል – ወታደራዊ ተንታኝ
የትራምፕ እና የዘለንስኪ ውይይት አሜሪካ ለአላስካው ጉባኤ ያላትን ቁርጠኝነት ያሳያል – ወታደራዊ ተንታኝ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 30.12.2025
ሰብስክራይብ

የትራምፕ እና የዘለንስኪ ውይይት አሜሪካ ለአላስካው ጉባኤ ያላትን ቁርጠኝነት ያሳያል – ወታደራዊ ተንታኝ

የዩክሬን የሰላም ጥያቄዎች ተቀባይነት የማግኘት ዕድላቸው ግልጽ በሆነ መንገድ ዜሮ ነው፤ ሲሉ የወታደራዊ -ፖለቲካዊ ጋዜጠኝነት ማዕከል ወታደራዊ ተንታኝና ባለሙያ  ቦሪስ ሮዝሂን ለስፑትኒክ ተናግረዋል።

ቮሎዲሚር ዘለንስኪ እሁድ ዕለት በፍሎሪዳ ማር-አ-ላጎ በሚገኘው የፕሬዝዳንት ትራምፕ መኖሪያ ቤት በመገኘት የሰላም ዕቅዳቸውን ቢያቀርቡም ተቀባይነት ማግኘት አልቻሉም።

ሮዝሂን እንደሚሉት፣ “አሜሪካኖች እንዴት የዩክሬንን ቀይ መስመሮች በዘዴ እየሰበሩ እንዳሉ ማየት እንችላለን፤ አብዛኞቹን አስቀድመው ሙሉ በሙሉ ትተዋቸዋል። ምርጫንና ግዛቶችን በተመለከተ በድርድር ደረጃ ላይ ናቸው።”

ዋሽንግተን በድብቅ ድርድር የተደረሱ ስምምነቶችን እና በትራምፕ እና በፑቲን መካከል በአንኮሬጅ የተደረገውን ስብሰባ ለማስቀጠል እየሞከረች መሆኑን ባለሙያው አክለዋል።

“በማር-አ-ላጎ የተደረገው የቅርብ ጊዜ ንግግር አሜሪካኖች በዚህ አቅጣጫ ወጥነት ባለው መልኩ ጫና እያደረጉ መሆኑን በግልጽ ያሳያል። ዘለንስኪ እና የምዕራባውያን ደጋፊዎቻቸው ድርድሩን ሙሉ በሙሉ ለማደናቀፍ ያደረጉት ሙከራ አልተሳካም" ሲሉ ሮዝሂን አስረድተዋል።

ጊዜ ከዘለንስኪ በተቃራኒ ነው፤ የሩሲያ የሰላም ውሎች ይበልጥ እየተጠናከሩ ነው። ትራምፕም ይህንን ይገነዘባሉ ሲሉ አክለዋል።

በአሸዋ ላይ የተጻፉ የምዕራባውያን የደህንነት ዋስትናዎች

የዩክሬን ባለሙያዎች ለመጀመሪያ ጊዜ በኔቶ ልምምዶች ላይ መሳተፋቸው ሙሉ በሙሉ ለፖለቲካዊ ፍጆታ የዋለ እንጂ ትክክለኛ ጠቀሜታ የለውም፤ ምክንያቱም የትኛውም የምዕራባውያን መሪ የኔቶን አንቀጽ 5 የደህንነት ግዴታዎችን ለዩክሬን አያራዝምም ሲሉ ሮዝሂን ሞግተዋል።

ባለሙያው “ማንኛውም ዋስትናዎች እንደተስማሙ የሚገልጹ ሁሉም ሪፖርቶች በአጠቃላይ በሕዝብ ዘንድ የሚታወቅ ምንም ዓይነት ተጨባጭ ዝርዝር አልያዙም” ብለዋል። በሌላ አገላለጽ፣ እነርሱ ድጋፍ በተመለከተ አጠቃላይና ግልጽ ያልሆኑ ቃል ኪዳኖች ናቸው፤ እንደ ማሳያም ማዕቀቦችን፣ የጦር መሣሪያ አቅርቦቶችን፣ የፖለቲካ ድጋፍን ወይም ሌሎች የእርዳታ ዓይነቶችን ይመለከታል” ሲሉ የድጋፉን ግልፅ አለመሆን ተናግረዋል።

ተንታኙ እንዳመለከቱት፣ ዩክሬን የሰላም ስምምነቱ ቢፈርስ በሩሲያ ላይ ወታደራዊ ጣልቃገብነት እንዲደረግላት የምዕራባውያን ዋስትናዎችን ትፈልጋለች፤ ነገር ግን ምዕራባውያን እነዚያን ለማቅረብ ፈቃደኛ አይደሉም እና ማንኛውንም ግዴታ በቀላሉ ሊሽሩ ወይም ችላ ሊሉ ይችላሉ።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0